አድምጥ! የሚጠራህ ማን ነው?

The listening lamb

የዮሐንስ ወንጌል 10፡ 1-18

አንድ ሰው ሲጠራህና የሚጠራህ ሰው ድምጽ ከየት አቅጣጫ እንደሚመጣ ለማወቅ ግራ ተጋብተህ ታውቅ ይሆን? ወይም ብዙ ጫጫታ መካከል ከመሆንህ የተነሳ የሚጠራህን ሰው ድምጽ ለመስማት ተቸግረህ ታውቅ ይሆን?

አድምጥ! አንድ ድምጽ እየጠራህ ነው፡፡ አዎ አንተን!

የተሟላ መልዕክት ክፍል አድምጥ! የሚጠራህ ማን ነው?

አንተ ማን ነህ? ስምህ ማን ነው? ከየት ነው የመጣኸው? የት ነው ምትኖረው? ወዴትስ እየተጓዝክ ነው?

የምትኖርበትን አካባቢ ስም ታውቃለህ፡፡ ድነገትም ከምትኖርበት አካባቢ ርቀህ ተጉዘህ አታውቅ ይሆናል፡፡ ነገር ግን የምትኖርበት አካባቢ የአንድ አገር አካል፤ አገራት ደግሞ የአለም አካል እንደሆኑ ታውቃለህ;፡፡

መጽሐፍ ቅዱስ

አለማችን ከተፈጠረች 6,000 ዓመታት ሆንዋታል፡፡ የተፈጠረችውም በእግዚአብሔር ነው፡፡ እግዚአብሔር ዓለምንና የመጀመሪያውን ሰው እንዴት እንደፈጠረ የተረከበት መጽሐፍ ቅዱስ የተባለ መጽሐፍ አለው፡፡ እግዚአብሔር ሰውን የፈጠረው በአምሳሉ ነው፡፡

ከዚያን ግዜ ጀምሮ ብዙ ልጆች ተወልደዋል፡፡ ብዙ ሰውችም ሞተዋል፡፡

አንተ የተወለድከው ከአባትና እናትህ ነው፡፡ ነገር ግን የሰራህ እግዚአብሔር ነው፡፡ እርሱ አንተን ብቻ ሳይሆን ሁሉን ነገር የፈጠረ አምላክ ነው፡፡ እግዚአብሔር ሁሉን ነገር እንዴት አድርጎ እንደ ሰራ እና አንተን እንዴት አድርጎ እንደፈጠረ አስበህ ታውቅ ይሆን? 

ወላጆችህ ስም አውጥተውልሀል፡፡ እግዚአብሔር ስምህን ያውቃል፡፡ በማንኛውም ቋንቋ ቢሆን እግዚአብሔር የእያንዳንዱን ሰው ስም ያውቃል፡፡ እርሱ ሁሉን አዋቂ ነው፡፡

እግዚአብሔር ፈጣሪያችን ስለሆን ስለ እኛ ሁሉን ያውቃል፡፡ እኛ የእርሱ ስለሆንን ይወደናል፡፡ እርሱ ከአባትና እናታችን ይልቅ አብልጦ የሚጠነቀቅልን በሰማይ የሚኖር አባታችን ነው፡፡

እግዚአብሔር

እግዚአብሔር የነበረ፣ ያለ እና ለዘላለም የሚኖር አምላክ ነው፡፡ ስለዚህም እስትንፋሱን በሰጠን ጊዜ እኛንም ለዘላለም እንድንኖር አድርጎናል፡፡ ነገር ግን ስጋችን ሟች ስለሆነ እርሱ ሳይሆን ለዘላለም የሚኖረው በውስጣችን የምትኖር ነብሳችን ነች ዘላለማዊ፡፡

እግዚአብሔርን ታውቀዋለህ? ድንገት “እግዚአብሔር ማን ነው? የትስ ነው የሚኖረው?” ብለህ ትጠይቅ ይሆናል፡፡

በእርግጥ ማወቅ ትፈልጋለህ? አዎ! በርግጥም ማወቅ ትፈልጋለህ፡፡ ውስጥህ በርግጥም ማወቅ ይፈልጋል፡፡

እግዚአብሔርን አይተኸው አታውቅም፤ ታውቃለህ እንዴ? አላየኸውም ማለት እኮ ታዲያ እግዚአብሔር የለም ማለት አይደለም፡፡

አንድ እግዚአብሔር ብቻ ነው ያለው፡፡ ከርሱ በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ ምክንያቱም እውነተኛ አምላክ በሰማይና በምድር የሚኖር አምላክ ነው፡፡ እርሱ በአንድ ጊዜ በሁሉም ቦታ ይገኛል፡፡

የእግዚአብሔር መኖሪያ የተዋበውና በላይ ያለው ሰማይ ነው፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር ድምጹን በሚታዘዙ ሰዎች ልብም ውስጥ ይኖራል፡፡

“እግዚአብሔርን ለማወቅ እንዴት መማር እችላለሁ?” የሚለውን ጥያቄ ትጠይቅ ይሆን? እግዚአብሔር እንዴት ልናውቀው እንደምንችል ድንቅ መንገድን አዘጋጅቶልናል፡፡

እግዚአብሔር ማን እንደሆነ እና ምን እንደሚመስል ለሰዎች ሁሉ እንዲያሳይ አንድያ ልጁ የሆነውን ኢየሱስን ከሰማይ ልኮታል፡፡ አብና ወልድ አንድ ናቸው፡፡

የእግዚአብሔር ልጅ በተአምራት ህጻን ልጅ ሆኖ ተወለደ፤ ትልቅም ሰው ሆኖ አደገ፡፡ ኢየሱስ ካደገ በኋላ ለሶስት ዓመታት ስለአባቱ ፍቅር ለሰዎች አስተማረ፡፡ ጨምሮም እግዚአብሔር ቅዱስ እንደሆነና ኃጢአትን እንደሚጸየፍ አስተማረ፡፡

ከዛም እግዚአብሔር ከኃጢአታችን የምንድንበትን መንገድ አዘጋጀልን፡፡ ልጁ ኢየሱስ በክፉዎች እጅ ወድቆ መስቀል ላይ እንዲሰቀል ፈቀደ፡፡ ኢየሱስ ከታላቅ ፍቅሩ የተነሳ ሕይወቱን ስለ እኛ አሳልፎ ሰጠ!

ኢየሱስ የዓለምን ሁሉ የኃጢአት ዋጋ ሊከፍል የቻለ መስዋዕት ነበር፡፡ አንተ ለሰራኸው ኃጢአት ሁሉ፤ ለትልቅ ለትንሹ፤ ለወንድ ለሴቱ ኃጢአት ሁሉ መስዋዕት የሆነው ኢየሱስ ነው፡፡

ኢየሱስ በመስቀል ላይ እንደተሰቀለ ቀረን? በመቃብርስ ተቀብሮ ቀረ? በፍጹም፣ ከሶስት ቀን በኋላ በድል ተነስቶ ወደ ሰማይ አረገ፡፡ የዚህች ዓለም ፍጻሜ በሚሆንበት ጊዜ የሰው ሁሉ ጻድቅ ፈራጅ ሆኖ ይገለጣል፡፡

የዮሐንስ ወንጌል ካለህ ምዕራፍ አስርን (10) አንብብ፡፡ ዮሐንስ ኢየሱስ ለህዝቡ ምን ያስተምራቸው እንደነበር ነው የጻፈው፡፡ ኢየሱስ ያን ጊዜ ለህዝቡ ያስተማረው ትምህር ዛሬ ለእኛም ትምህርት ነው፡፡ ኢየሱስ መልካም እረኛ እንደሆነ እና ነፍሱንም ስለ በጎቹ አሳልፎ እንደሰጠ ተናግርዋል፡፡ በጎቹ ደግሞ እኛ ነን፡፡ በጎቹ የሆኑት ድምጹን ያውቃሉ፡፡ እያንዳንዳቸውን በስም ይጠራቸዋል፤ እነሱም ሌላውን ከመከተል ይሸሻሉ፡፡

እንግዳው፤ ሌላኛው ድምጽ

እንግዳ የተባለው እና ልንሸሸው የሚገባው ማንን ነው? ኦ! ሌባውን ነው፡፡ እርሱ ስለ በጎቹ ምንም ደንታ የለውም፡፡ ውሸታም ስለሆነ አንዳች እውነት በእርሱ ዘንድ የለም፡፡ እርሱ ዲያብሎስ ነው፤ እርሱ ጠላታችን የሆነው ሰይጣን ነው፡፡

አስቀድሞ እርሱ የእግዚአብሔር ጠላት ነው፡፡ በአንድ ወቅት ከእግዚአብሔር ጋር በሰማይ ይኖር የነበረ ቅዱስ መልአክ ነበር፡፡ ነገር ግን በትዕቢት እራሱን ከእግዚአብሔር በላይ ከፍ ሊያደርግ ሞከረ፡፡ ከእግዚአብሔር ጋር ተዋጋ፣ ብዙ መላእክትም ተባበሩት፡፡ እግዚአብሔር ኃያል ስለሆነ ድል በመንሳት ሰይጣንን ከነተከታዮቹ ከገነት አባረራቸው፡፡ ከዚህም የተነሳ ሰይጣንን እግዚአብሔርን ይጠላዋል፡፡

ሰይጣን እግዚአብሔር አጠገብ መቅረብ ስለማይችል እግዚአብሔር በአምሳሉ በፈጠራቸው ሰዎች ላይ ተቆጣ፡፡ ሰይጣን ኃጢአተኛ ስለሆነ ሰው ሁሉ ኃጢአት እንዲሰራ ያባብላል፡፡ ኃጢአት ዳግመኛ ወደ ገነት ሊገባ ፈጽሞ አይችልም፡፡

እግዚአብሔር ለዲያብሎስ እና መላእክቱ ሁሉ የሰራው ሌላ ስፍራ አለ፡፡ ይህ ስፍራ ሲኦል ነው፡፡ ሲኦል እሳቱ የማይጠፋ  የስቃይ ቦታ ነው፡፡ ዲያብሎስ እና ተከታዮቹ ሁሉ ለዘላለም የሚቀጡበት ቦታ ነው፡፡ እኛም የሰይጣንን ድምጽ ለመስማት የምንመርጥ ከሆነ እግዚአብሔር ወደዚህ ቦታ ይልከናል፡፡

ሰይጣን ስለ ሲኦልም ሆን ስለ እግዚአብሔር እንድናስብ አይፈልግም፡፡ ስለ እግዚአብሔር እንድናስብ ስለማይፈልግ ስለ እግዚአብሔር የሆኑ ሀሳቦቻችንን ሁሉ በመስረቅ የእርሱን ድምጽ እንድንሰማ ሊያደርገን ይሞክራል፡፡

በውስጥህ ያን የተለየውን የእንግዳውን ድምጽ ሰምተህ ታውቃለህ?

ሰይጣን አንዳንዴ መልካም ነገር እንደሚሰጠን አድርጎ ያሳምነናል፡፡ አንዳንድ ጊዜ “እኔ ከሌሎች የተሻልኩ ነኝ፤ እኔ ከማንም በላይ አስፈላጊ ሰው ነኝ፤ ቅድሚያ ለእኔ ነው የሚገባው፤ አለቀውም/አለቃትም፤ ለመብቴ መታገል አለብኝ፤ በቂ ስለማላገኝ ብሰርቅም ችግር የለውም፤ ሁሉ ስለሚዋሹ እኔም ብዋሽ ችግር የለውም፤ ምን እያሰብኩ እንደሆነ ማንም ስለማያውቅ ጸያፍ ሀሳቦችን ባስብ ምንም ችግር የለውም፤ በብልግና የተሞሉ ቃላት በጣም ስለሚያስቁ ምንም ችግር የለባቸውም” ብለን እንድናስብ ያደርገናል፡፡

በሌላ ጊዜ ደግሞ ተስፋ አስቆርጦን “የማልረባ ነኝ፤ በሕይወት መኖሬ ምንም ትርጉም የለውም” ብለን እንድናስብ ያደርጋል፡፡

እነዚህ ሁሉ የዲያብሎስ ድምጾች ናቸው፡፡ እርሱ ውሸታም ነው፤ እኛንም ውሸታሞች ሊያደርገን የሚጥረው ለዚህ ነው፡፡ እርሱ ሌባ ነው፤ እኛም እንድንሰርቅ የሚፈልገው ለዚህ ነው፡፡ እርሱ ነፍሰ ገዳይ ነው፤ እኛም ሌሎችን የምንጠላ ሰዎች ሊያደርገን የሚጥረው ለዚህ ነው፡፡

ይህንን አይነቱን ድምጽ ስትሰማ ምን ዓይነት ስሜት ይሰማሀል? ውስጥህን ደስ ያሰኝህ ይሆን? ኦ! በፍጹም ደስታ እንዳይሰማህ ያደርጋል፡፡ መደበቅ እንድትፈልግ ያደርግሀል፡፡ ሰይጣንም ልክ እንደዚህ ነው፤ ነገሮችን በጨለማ ተደብቆ ማድረግ ነው የሚወደው፡፡

ኢየሱስ፤ የእረኛው ድምጽ

መልካሙን እረኛ ኢየሱስን ታውቀዋለህን? የእርሱ በግ መሆን ትፈልጋለህን? ድምጹን ማወቅ ትፈልጋለህን?

አዎ ትችላለህ፡፡ ነገር ግን በመጀመሪያ ያንን ሌላኛውን ድምጽ መስማት ማቆም አለብህ፡፡

በጸጥታ ውስጥ ሆነህ ስታዳምጥ ኢየሱስ ዝግ ባለ ድምጽ ሕይወትህን አሳልፈህ እንድትሰጠው ጥሪን ሲያቀርብልህ ትሰማዋለህ፡፡ ኃጢአትህን ሁሉ ተናዘህ ንስሀ እንድትገባ ሲነግርህ ትሰማዋለህ፡፡    

አንዳንድ ጊዜ ተረጋግተህ ተቀምጠህ ሳለ “ችግሮቼን እና ሸክሞቼን ምን ላድርጋቸው? መልካም ሰው ብሆን እመኛለሁ፤ የማልታመምበት ወይም የማልራብበት ቦታ ብኖር ማናለ፤ ስሞት ምን እሆናለሁ?” የሚሉ ሀሳቦች አስበህ ሊሆን ይችላል፡፡

ድንገት ከእነዚህ የበለጡ ብዙ ሀሳቦች አስበህ ሊሆን ይችላል፡፡ ይህ ድምጽ ኢየሱስ አንተን እየተጠራ ያለበት ድምጽ ነው፡፡

አንዳንድ ጊዜ ምክንያቱን ሳታውቀው የሀዘን ስሜት ይሰማህ ይሆን? ወይም ሰው አብሮህ እያለ የብቸኝነት ስሜት ይሰማህ ይሆን? ይህ የሚሆንበት ምክንያት የፈጠረህና ሚወድህ እግዚአብሔር አብሮህ ስላልሆነ ሊሆን ይችላል፡፡ እርሱ የጠፉትን በጎቹን የሚፈልግ እረኛ ነው፡፡ ደጋግሞ እየጠራህ እና እየፈለገህ ነው!

የእረኛውን ድምጽ ስትሰማ መልስን ስጠው፡፡ ከኃጢአትህ ነጻ መውጣት እንደምትፈልግ ንገረው፡፡ የሚሰማህን ንገረው፤ እንዲያድንህም ጠይቀው፡፡ ጸሎት ማለት እንደዚህ ነው፡፡

ወደ ሰማይ አምላክ እግዚአብሔር ጸልየህ ታውቅ ይሆን? አሁኑኑ ጸልይ፡፡ እርሱ ይሰማሀለ፤ ይረዳህማል፡፡ ዘወትር የምትናፍቀውን ሰላም ይሰጥሀል፡፡

የእርሱ በግ በመሆን ድምጹን ማወቅ ትፈልጋለህ? እርሱ ወዳጅህ ሊሆንህ እና ከኃጢአት ሸክምህ ሊያሳርፍህ ይፈልጋል፡፡ ያን ጊዜ ውስጥህ በደስታ ይሞላል፤ እንደ እርሱም አፍቃሪ እና ቸር ትሆናለህ፡፡ ፍራቻዎችህን ሁሉ ድል እንድትነሳ ይረዳሀል፡፡

ሌሎች ክርስቲያን በመሆንህ ቢያሾፉብህም አንተ ግን ኢየሱስ እንደሚጠነቀቅልህ ትረዳለህ፡፡ እንግዳው እየመጣ ቢፈትንህም ኢየሱስ እንድታሸንፈው እንደሚረዳህ ልታምነው ይገባል፡፡

በእረኛው የፍቅር እቅፍ ውስጥ ስታርፍ፣ እርሱ በመጨረሻ ድንቅ ወደ ሆነውና በደስታ ወደ ተሞላው ቤቱ ከእግዚአብሔር ጋር ለዘላለም እንድትኖር እንደሚወስድህ ትረዳለህ

ለተጨማሪ መረጃ ያግኙን

በረሪ የውንጌል ጽሑፎችን (ትራክቶችን) ለማዘዝ

ምን ያህል ታማኝ ነህ?

“እነሆ፥ እውነትን ወደድህ፤ የማይታይ ስውር ጥበብን አስታወቅኸኝ” (መዝሙር 51፡6)

ታማኝነት የእውነተኛ ህይወት መገለጫ ባህርይ ነው፡፡ ታማኝነት በዋናነት የልብ ጉዳይ ነው፡፡ ታማኝነት ከኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል መሰረታዊ መመሪያዎች አንዱ ነው፡፡ እግዚአብሔር የልብን ሀሳብና መሻት ያውቃል፡፡ እውነተኝነት ለእግዚአብሔር መሰረታዊ መርህ ነው ምክንያቱም እርሱ የእውነት አምላክ ነው (ዘዳግም 32፡4)፡፡ ሙሉ በሙሉ ታማኝ የሆነ ልባችንን በእርግጥም ይባርካል፡፡

የሚታወቅብህ ከመሰለህ እውነትን፤ ማንም ማያውቅብህ ከሆነ ግን ውሸትን ትናገራለህን?

ሆን ብለህ ሰዎችን ወደ ተሳሳተ አመለካከት ትመራቸዋለህ?

መክፈል እንደማትችል እያወቅህ እዳ ውስጥ ትገባለህ?

ስትፀልይ ያለህበትን ሁኔታ በግልጽ ለእግዚአብሔር ትናገራለህ?

እግዚአብሔር እንድታደርግ ያሳወቀህን ሁሉ በታማኝነት ታደርጋለህ?

የተሟላ መልዕክት ክፍል ምን ያህል ታማኝ ነህ?

ለመጽሀፍ ቅዱስ አትተምሮዎች ታማኝ ነህ?

በሰዎች ፊት ሆነህ እንደምትቀርበው ዓይነት ሰው ነህን?

በአዲስ ኪዳን ውስጥ ሐናንያ እና ሰጲራ ስለሚባሉ ባልና ሚስት የተጻፈ አስደናቂ ታሪክ አለ (ሐዋ. ስራ 5፡1-11)፡፡ ሌሎች  ብዙዎች ያደርጉ እንደነበረው እነርሱም መሬታቸውን ሸጡ፤ ከሚስቱም ጋር ከሽያጩ እኩሌታውን ለማስቀረት በስውር ተስማምተው ሳለ ሙሉ ገንዘቡን ለቤተ ክርስቲያን የሰጡ አስመሰሉ። ሐናንያና ሰጲራ መሬታችንን ይህን በሚያህል ዋጋ ሸጥነው በማለት ገንዘቡን ለቤተ ክርስቲያን መሪዎች አመጡ፡፡ ለማታለል በመሞከራቸው እግዚአብሔር ወዲያውኑ በሞት ቀጣቸው፡፡ የቀደመችው ቤተ ክርስቲያን ታሪክ በሆነው በዚህ ክስተት ላይ ግብዝነት ወይም አለመታመን ለጥብቅ ቅጣት ሲያጋለጥ እናያለን፡፡ እግዚአብሔር እንዲህ ያለውን ሀሰተኝነት አጥብቆ ይቃወማል፡፡ እኛም እንደ ሐናንያና ሰጲራ ሰዎች ስለኛ የተሳሳተ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ልናደርግ እንችላለን፡፡ ለድርጊቶቻችን በእግዚአብሔር ፊት ተጠያቂ እንደምንሆን እንዘነጋለን፡፡ እግዚአብሔር ልባችንን ስለሚያውቅ ፍጹም ታማኝነትን ከኛ ይፈልጋል፡፡

ግብዝ የሆነ ሰው ያልሆነውን እንደሆነ ያስመስላል፡፡ እውነተኛ ነኝ ይላል ነገር ግን ለጥቅሙ ሲሆን እውነታን ከማጋነን ወደ ኋላ አይልም፡፡ ችግረኞችን ስለመርዳት ያወራ ይሆናል ነገር ግን አደጋዎች ሲከሰቱ ጊዜና ገንዘቡን ለመለገስ ፈቃደኛ ይይደለም፡፡  አንድ ሰው የባልንጀራው ሁኔታ ከልቡ እንዳሳዘነው ሊያስመስል ይችላል ነገር ግን በችግር ወስጥ ያለ ባልነጀራውን ከመርዳት ይልቅ ማማት ይቀለው ይሆናል፡፡ አንድ ሰው ታማኝ መስሎ ሊቀርብ ይችላል ነገር ግን እስካልታወቀበት ድረስ የሌላውን ሰው ገንዘብ ለመውሰድ ወደ ኋላ የማይል ሰው ሊሆን ይችላል፡፡ አታላይም ሆኖ ሳለ በአስተሳሰቡ ብልጠት ከብዙ ሰዎች እንደሚሻል አድርጎ ራሱን ለማሳመን የሚጥር ይሆናል፡፡ ከነዚህ ሁኔታዎች በአንዱ የተገኘ ሰው ታማኝ እንዳይደለ ወይም ግብዝ መሆኑን ያሳያል፡፡

የሰዎች ግብዝ ባህርይ እግዚአብሔርን ሁልጊዜ ያሳዝናል፡፡ “ይህ ሕዝብ በከንፈሩ ያከብረኛል፥ ልቡ ግን ከእኔ በጣም የራቀ ነው” (ማቴዎስ 15፡8)፡፡ ለሰው በአፉ የሚናገረውንና በልቡ ያለውን ማስታረቅ ከባድ ነው፡፡ ከውስጥ ማንነታችን የሆነ ታማኝነት በጌታ ፊት ተቀባይነትን እና ፀጋን ለማግኘት ቁልፍ ነው፡፡

እውነተኛ ክርስቲያን የታማኝነት ምሳሌ ነው፡፡ በእግዚአብሔር ፊት ባለው ታማኝነት መጠን በመንፈሳዊ ሕይወቱ ያድጋል፡፡ አጠገባችን ካሉ ሰዎች ጋር ባለንም ግንኙነት ታማኝነት ጥንቃቄና አትኩሮት ሊሰጠው ያስፈልጋል፡፡ በቃላችንም ሆነ ተግባራችን አንዳችን በሌላችን ላይ እምነት የሚጣልብን ልንሆን ያስፈልገናል፡፡ ስለ እውነት የሚጠበቅብንን መስዋዕት ሁሉ ለመክፈል ፈቃደኞች ልንሆን ያስፈልገናል፡፡

ከሚቀጥለው ታሪክ ልንማር የምንችለው ትምህርት አለ፡፡ አንድ መምህር አንድን ልጅ እንዲህ ብላ ጠየቀችው “ለአንድ ብር ብለህ ውሸትን ትናገራለህ ?”

“አልናገርም መምህር” ሲል መለሰ ትንሹ ልጅ፡፡

“ለአምስት ብርስ ብለህ ውሸት ትናገራለህ?”

“አልዋሽም” አለ ልጁ፡፡

“ለአስር ብር ብለህ ውሸት ትናገራለህ”

“አልዋሽም” ነበር መልሱ፡፡

“ለአንድ ሺህ ብር ብለህስ ውሸት ትናገራለህ?

“ወይኔ” አለ በውስጡ “በአንድ ሺህ ብር ማድረግ የማልችለው ምን አለ?”

በማመንታት ላይ ሳለ ከኋላው የነበረ አንድ ሌላ ልጅ “አላደርገውም” አለ፡፡

“ለምን?” ጠየቀች መምህሯ፡፡

“ምክንያቱም ውሸት ይጣበቃል፤ አንድ ሺህ ብሩ ሲያልቅ፣ ከብሩ የሚገኘው ጥሩ ነገር ሁሉ ሲቆም ውሸቱ ግን እዛው እንደተጣበቀ ይቀራል”

እውነት ምቾት ቢነሳንም እንኳን ልንጠብቀው ፈቃደኞች ልንሆን ይገባል፡፡ ከጊዜያዊ ሀፍረት ራሳችንን ለማዳን ብለን መዋሸት ሀቀኝነታችንን አሳልፈን በመስጠት የምንከፍለው ትልቅ ዋጋ ነው፡፡ እምነትን በማጉደል የሚገኝ ገንዘብ ለቆሸሸ ህሊና እና በዚህ አይነቱ ኃጢአት ላይ እግዚአብሔር ለሚያኖረው ዘላለማዊ ፍርድ የሚከፈል ትንሽ ዋጋ ነው፡፡ 

ከታች የተዘረዘሩት ዓይነት ክፉ ስራዎች እየሰራህ በእግዚአብሔር ብርሀን እመላለሳለሁ ትላለህን?

  • ወንድም እና እህቶችህን ይቅር አለማለት
  • ሰዎችን አሳዝነህ ጥፋትህን አለማረም
  • እውነትን ማጋነን
  • ቃልህን አለመጠበቅ
  • የእግዚአብሔርን መባ እና አስራት መስረቅ

ታማኝነት የባህርይ መመዘኛ ነው፡፡ እግዚአብሔር ልባችንን ያውቃል፤ ከፊቱም የተሰወረ ምንም ነገር የለም፡፡ ይሁን እንጂ አንዳንድ ጊዜ እግዚአብሔር እንደሚያውቀን እና በውስጣችንም እንደሚሰማን ሆነን በእግዚአብሔር ፊት አንቀርብም፡፡ ታማኝነታችንን ወይም እውነተኛ ማንነታችንን  በሰዎች ፊት አንገልጠው ይሆናል፡፡ እውነተኛ ደስታ ያለው ሰው ለእግዚአብሔር ታማኝ የሆነና ትክክለኛ ማንነቱን የማይደብቅ ነው፡፡ ልባችንን ለእግዚአብሔር ግልጽ ስናደርግ እነዚህ ችግሮች መፍትሄን ያገኛሉ፡፡

አመለካከታችን እና መነሻ ሀሳባችን የታማኝነት ፈተናን ማለፍ አለባቸው፡፡ ይህንን ፈተና በእግዚአብሔር እና ሰዎች ፊት ለማለፍ ውስጣዊ የሆነ ለውጥ ያስፈልገናል፤ ምክንያቱም ውጫዊው ማንነታችን  የውስጣዊው ማንነታችን መገለጫ ነውና፡፡ ታማኝ ነህ? ታማኝነታችንን፤ እግዚአብሔር ይሻልዋል፣ ሌሎች ይጠብቁብናል፣ እኛም ተጠቃሚ እንሆንበታለን፡፡ የታማኝነት ህይወት ዋጋው እጅግ የከበረ ነው፡፡ “በነገር ሁሉ በመልካም እንድንኖር” ወደናል (ዕብራውያን 13፡18)፡፡ “ለማንም ስለ ክፉ ፈንታ ክፉን አትመልሱ፤ በሰው ሁሉ ፊት መልካም የሆነውን አስቡ” (ሮሜ 12፡17)፡፡  በተጨማሪ ዘሌዋውያን 19፡35-36 እና ምሳሌ 19፡5ን አንብብ፡፡

ለተጨማሪ መረጃ ያግኙን

በረሪ የውንጌል ጽሑፎችን (ትራክቶችን) ለማዘዝ

በየትኛው መንገድ ልጓዝ?

ህይወት እንደ ጉዞ መሆኑን ታውቅ ነበር? የህይወት ጉዞ ወደ ሁለት ቦታ የሚያደርሱ ሁለት ጎዳናዎች አሉት፡፡ በየትኛው መንገድ ላይ ለመጓዝ መምረጥና መወሰን የአንተ ነው፡፡

በአንድ ቤተሰብ ውስጥ ልጅ ሲወለድ የህይወትን ጉዞ ይጀምራል፡፡ በሰማይ የሚኖር አምላክ ለታዳጊ ልጆች ልዩ መንገድን ያደርጋል፡፡ ይሄ መንገድ የየዋህነት፣ እራስን ወደ ማወቅ የሚያመጣ መንገድ ነው፡፡ በዚህ መንገድ ላይ እናትና አባት ለልጆች ስለ ህይወት በማስተማር መሪዎች ናቸው፡፡

በልጅነት በዚህ መንገድ ላይ ለተወሰነ ጊዜ በንፅህና ትጓዛለህ፤ ነገርግን በኋላ ላይ ወደ መንታ መንገድ ትደርሳለህ፡፡ የልጅነት እና የአለማወቅ ጎዳና ያበቃል፤ ከዚያም ወደ የተለያዩ ቦታ የሚወስዱ ሁለት መንገዶች ፊት ትመጣለህ፡፡ እስከ እዚህ ጊዜ ድረስ ወላጆችህ መሪዎችህና በዋናነት ውሳኔዎችህን ሲወስኑልህ ቆይተዋል፡፡ ወደዚህ መስቀለኛ መንገድ ከመጣህ በኋላ ውሳኔው የአንተ ሆንዋል፡፡ የትኛውን መንገድ ልምረጥ? ይህ ውሳኔ እጅግ ዋና፣ ከሁሉ በላይ የህይወትህ ትልቅ ውሳኔ ነው፡፡ ይህ ውሳኔ እጅግ ዋና የሆነበት ምክኒያት አንደኛው መንገድ መልካም፣ ንፁህ ህይወት፣ በደስታ የተሞላ ወደ መንግስተ ሰማይ የሚመራ መንገድ ነው፡፡ ሌላንኛው  የሀጢአተኝነት እና የክፋት መንገድ፣ በሀዘን የተሞላ፣ ወደ ገሀነም የሚመራ ነው፡፡

ወደ እነዚህ መንገዶች መድረሴን አንዴት ማወቅ እችላለሁ? የተቀመጠ ህግ ወይም እድሜ የለም፡፡አንዳንድ በልጅነት ጎዳና ላይ ያሉ ልጆች በህይወታቸው ከሌሎች ቀድመው ወደ መስቀለኛው መንገድ ይደርሳሉ፡፡ ምናልባትም መስቀለኛ መንገዶቹ ሰውየው ወንጌልን እስከሰማበት ጊዜ ድረስ ወይም የተሸለ መንገድ እንዳለ እስከሚረዳበት ጊዜ ድረስ አይደረስባቸውም ይሆናል፡፡ ምናልባትም ለብዙዎች ወንጌል በሰሙበት ሰእት የልባቸው መምታትና የመክበድ ስሜት ሊሆን ይችላል፡፡ ትክክል ስለ ሆነው እና ስላልሆነው ግንዛቤ ወይም ጌታን ለመከተል መሳብ ሊሆን ይችላል፡፡ እነዚህ የመስቀለኛ መንገዶች ምልክት ናቸው፡፡ በሁሉም ሁኔታ እግዚአብሔር የፍቅር አምላክ ስለሆነ የሁለቱን መንገዶች ምንነት ያሳውቀናል፡፡ ጠባቡ መንገድ በየትኛውም አገር እና ባህል ውስጥ ለሚኖር ፍጹም እንደሆነ ይገልጥለታል፡፡

በመስቀለኛው መንገድ ፊት ቆመህ ምን ትመለከታለህ?

ሁለቱን መንገዶች በደንብ አስተውላቸው፡፡ መጀመሪያ ላይ ሁለቱም መንገዶች አትኩሮትን የሚስቡ ናቸው፡፡ ቀረብ ብለህ ስታስተውል አንደኛው መንገድ ሰፊ ደግሞም ለመጓዝ ምቹና ቀላል እንደሆነ ታያለህ፡፡ ሌላንኛው መንገድ ጠባብ በተላያዩ ቦታዎች ኮሮኮንችና ዳገታማ የሆነ ነው፡፡ ሰፊው መንገድ ብዙ ብዙ ሰዎች የሚጓዙበት ነው፡፡ ጠባቡ ጥቂት ሰዎችን ብቻ ይዟል፡፡ ትክክለኛውን መንገድ መምረጥ እጅግ በጣም አስፈላጊ ነው፡፡

ግራ ተጋብተሃል እና የትኛውን መንገድ መምረጥ እንዳለብህ እርግጠኛ አይደለህም? ብዙ ተጓዥ ወዳለው ሰፊ መንገድ ጠጋ ስትል የመንገዱ መሪና ጌታ ከእርሱ ጋር እንድትጓዝ ሲጠይቅህ ትሰማለህ፡፡ በመጀመሪያ መንገዱ የጠባቡን መንገድ አይነት ይመስላል፡፡ በዚህ መንገድ ላይ ጉዞ የሚጀምሩ መልካም ሀሳብ አላቸው፡፡ ብዙዎች ለጊዜው በዚህ መንገድ ላይ ካሉ ወጥመዶች መቆጠብ ይችላሉ፡፡ የመሪው ታሪክ አርቴፊሻል ቢሆንም ለጆሮ ደስ የሚልና የሚያባብል ነው፡፡ በጉዞው መሀል ብዙ ጓደኞችን ያቀርብልሀል፤ ማንም ግን ከልቡ ደስተኛ አይመስልም፡፡ በዚህ መንገድ ላይ ያሉ መዝናኛዎች ገደብ የላቸውም፡፡ መጠጣት፣ ማጨስ፣ መጨፈር፣ፓርቲዎች እና ሌሎች ብዙ መዝናኛዎች አሉት፡፡ ግብረገብነትና ስነ ስርአት ቦታ አይኖራቸውም፡፡ ውሸት፣ ስርቆት እና ማታለል የተለመዱ ተግባሮች ናቸው፡፡ በዚህ መንገድ ላይ የፈለግከውን አይነት የህይወት ስታይል ትመርጣለህ፡፡ እንዳሰኘህ መሆን ትችላለህ፡፡ ነፃነት ይሉታል፡፡ ይህ መንገድ ብዙ ይዞህ ይጓዛል እናም ምቹ ስለሚመስል እያባከንክ ያለኸውን ጊዜህን አታስተውለም፡፡ በዚህ ጎዳና ላይ ያሉ ብዙ ሰዎች ለብዙ የተወሳሰቡ ነገሮች ባሮች ከመሆናቸው የተነሳ መውጫ መንገድ አይታያቸውም፡፡ ተስፋ መቁረጥ፣ ሀሽሽ (ሱስ)፣ ግድያ እና ራስን ማጥፋት ውጤቶቹ ናቸው፡፡

የተሟላ መልዕክት ክፍል በየትኛው መንገድ ልጓዝ?

በህይወትህ የምትፈልገው ይህን ነው? መጓዝ የምትፈልገው በዚህ ጎዳና ላይ ነው? የዚህ መንገድ መሪ በመንገዱ የመጓዝ የመጨረሻ እጣ ፈንታ ምን እንደሆነ ምንም አመማሳወቁን  አስተውለሀል? አያደርገውም፤ እራሱን አይክድም፡፡ የበግ ልብስ የለበሰ ተኩላ ሰይጣን ነው፡፡ በሰፊው መንገድ ላይ ለመጓዝ የሚከፍለው ብድራት የማይጠፋ የእሳት ባህር ሲኦል ነው፡፡ ይህ ቦታ የተዘጋጀው ለዳቢሎስና ለጭፍሮቹ ነበር፡፡ በዚያ ለዘለአለም ልቅሶ፣ ዋይታ እና ጥርስ ሟፏጨት ይሆናል፡፡ አንተስ? ከእርሱ ጋር ተጉዘህ የሲኦልን ብድራት መቀበል ትፈልጋለህ?

ጠባቡን መንገድ ቀረብ ብለህ ተመልከተው፡፡

ይህ መንገድ ከሰፊው መንገድ በእጅጉ ይለያል፡፡ ዳገታማ መንገድ እና ኮረብታና ሸለቆዎች በተለያዩ ቦታዎች ያሉት ነው፡፡ ፀሀይና ሙቀት አለበት ነገርግን መንገዱን ይዘህ ከሄድክ ጥምን ወደሚያረካ ምንጭ ትደርሳለህ፡፡ በዚህ አረፍት ታደርጋለህ፣ ውሀን ትጠጣለህ፡፡ ከጅረቶቹም መሚፈሰው ውሀ በመንገድ የደከሙ እግሮችህን ታርሳለህ፡፡ ታድሰህ መንገድህን ትቀጥላለህ፡፡ የሚወጡ ተራሮችም አሉት፤ አንዳንዴም መንገዱ የደበዘዘ ሊመስል ይችላል፡፡ በመንገድህ ስትቀጥል ወደ ተራራ ጫፍ ትደርሳለህ ከዚያም ለምለምና አረንጓዴ ወደ ሆነ ሸለቆ ይመራሀል፡፡ በጠባቡ መንገድ ላይ ያሉ ወዳጆችህ ሁሉ ክርስቲያኖች ናቸው፡፡ ወንድምና እህት ይሆኑሀል፡፡ ይወዱሀል፣ ይጠነቀቁልሀል፡፡ በመንገድህ ተደናቅፈህ ስትወድቅ ተመልሰህ በእግሮችህ እንድትቆም ያግዙሀል፡፡ የሚረዱህና ደጎች ናቸው፡፡ ከሁሉም የሚበልጥ መሪና የግል ወዳጅ ግን አለህ፡፡ እሱ ጌታ ነው፤ መልካሙ እረኛ (መዝሙር 23)፡፡ በጣም ስለሚወድህ ከጎንህ በመሆን በጠባቡ መንገድ አብሮህ ይጓዛል፡፡ መንገድህ የጨለመና ከባድ ሲሆንብህ እጅህን ይዞ በግለጽ ማየት እስክትችል ይመራሀል፡፡ ተጓዡ ሲደክመው እና መንገዱም አደገኛ ሲሆን  እረኛው በክንዶቹ ይሸከምሀል፡፡ ከጊዜ በኋላ በእግርህ መንገዱን ለመቀጠል ከድካምህ ትበረታለህ፡፡ በጠባቡ መንገድ የምትጓዘው እንዲህ ይሆናል፡፡

 እነዚህ ጠባብና ሰፊ የሆኑ ሁለት መንገዶች  በህይወት ጉዞ መጨረሻ ላይ ይጠናቀቃሉ፡፡ በመንገዶቹ መጨረሻ ሞትን እንጋፈጣለን፡፡ አንዳንድ ጊዜ ሞት ማለት  ወንዝ መሻገር ነው ይባላል፡፡ ሁሉም ሰው ይሻገረዋል፡፡ ከዚያ በኋላ ፍርድ ይሆናል፤ እግዚአብሔር አራሱ ስለ ተጓዝንበት መንገድ ፍርድ ይሰጣል (እብራውያን 9፡27)፡፡

እነዚያ በሰፊው መንገድ ላይ ከሰይጣን ጋር እየመራቸው ሲጓዙ የነበሩት የመሻገሪያ ወንዙን አስፈሪ ሆኖ ያገኙታል፡፡ ለምን? ወንዙን አብረውት የሚሻገሩት የላቸውም፡፡ ወዳጆቻቸው ሞትን የሚፈሩ ናቸው፡፡ ብቻቸውን መሻገር ይኖርባቸዋል፡፡ ከዚያም በገሀነም እውነታ ፊት ይነቃሉ፤ ለጥልቀቱ መጨረሻ በሌለው በማይጠፋ የእሳት ባህር ውስጥ ራሳቸውን ያገኙታል፡፡

የበጠባቡ መንገድ ተጓዥ ከሆንክ ግን የመሻገርያ ወንዙን ትናፍቃለህ፤ ከወንዙ ማዶ አክሊልህ ይጠብቅሃል፡፡ ጊዜው ውብ ነው፤ ሰላማዊ ጊዜ፤ መልካሙ እረኛ በሞት ወንዝ መርቶ ያሻግርሃል፡፡ ከዚያ በሰማያዊ መኖሪያህ፤ በዚያ ጎዳናዎቹ በወርቅ የተሰሩ፣ ቃላት ሊገልጸው የማይችል የመላእክት ዝማሬ ባለበት ትሆናለህ፡፡ ከዚህ በኋላ የምትወጣቸው ዳገቶች አይኖሩም፣ የምትሻገራቸው ሸለቆዎችም የሉም፤ ሰላም፣ ጸጥታ እና ደስታ ከዘለአለም እስከ ዘለአለም ብቻ ይሆናል፡፡ መሪ ጌታህ ደግሞ ከአንተ ጋር ይሆናል፡፡ “እንባዎችንም ሁሉ ከዓይኖቻቸው ያብሳል፥ ሞትም ከእንግዲህ ወዲህ አይሆንም፥ ኀዘንም ቢሆን ወይም ጩኸት ወይም ሥቃይ ከእንግዲህ ወዲህ አይሆንም፥ የቀደመው ሥርዓት አልፎአልና” (ራዕይ 21፡4)፡፡

የትኛውን መንገድ ትመርጣለህ? ምላሽህ ምንድን ነው? የምትመርጠው ምርጫ በጣም ወሳኝ እንደሆነ አስታውስ፡፡ መንግስተ ሰማይ ወይስ የገሀነም እሳት ነው፡፡ ጠባቡን መንገድ ምረጥ፣ ጌታም እንዲረዳህ ጠይቀው፡፡ “በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ፥ መንገዱም ትልቅ ነውና፥ ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው ወደ ሕይወት የሚወስደው ደጅ የጠበበ፥ መንገዱም የቀጠነ ነውና፥ የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው” (ማቴዎስ 7፡13-14)፡፡

ለተጨማሪ መረጃ ያግኙን

በረሪ የውንጌል ጽሑፎችን (ትራክቶችን) ለማዘዝ