ለመዳናችን በግል ማስረገጫ

መጽሐፍ ቅዱስ ሰዎች ብዙ ጊዜ “በግል መዳናችንን ማስረገጥ እንችላለን ወይስ አንችልም?” ብለው ለሚጠይቁት ጥያቄ መልስ ይሰጠን ይሆን? አንድ ሰው ኃጢያቱ ይቅር እንደተባለለት ያውቅ ይሆን? ወይስ ለማወቅ የፍርድ ቀን እስኪመጣ መጠበቅ ይኖርበታል? ይህን ወሳኝ ጥያቄ ለመመለስ እስከዚያን ቀን መቆየቱ አለመታደልና በጣም አደገኛ ውሳኔ ነው፡፡

አዎን፤ የፈለገ ሰው ማወቅ ይችላል፡፡ ጌታም ስለመዳናችን እርግጠኛ እንድንሆን ይፈልጋል፡፡ “እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ” (ማቴ. 11፥28) እያለ ጥሪውን እያቀረበልን ነው፡፡ በዮሐ.3፥16 “በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን (ኃጢያተኛውን፤ ሁሉንም) እንዲሁ ወዶአልና” ሲል ይነግረናል፡፡ ሰው ሁሉ ከፍጥረቱ ኃጢያተኛ በመሆኑ የእግዚአብሔርን ፍቃድ ከማድረግ ጎድሏል፡፡

ሰው በዚህ ባልተለወጠ ሁኔታው አዳኝ ያስፈልገዋል፡፡ በኃጢያቱና በመተላለፉ የሞተ በመሆኑ ከጥፋቱ የሚያድነው አዳኝ ያስፈልገዋል፡፡ ቸር እና መሀሪ የሆነው የሰማይ አምላካችን ለአስደናቂ ጸጋው እራሳቸውን አሳልፈው ለሚሰጡ ሁሉ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ድነትን አዘጋጅቶላቸዋል፡፡ ኢየሱስ ደሙን በማፍሰስና “የኃጢአታችን ማስተሰሪያ” (1ኛ ዮሐ. 2፥2) በመሆን በመስቀል ላይ ሞቶልናል፡፡ ኃጢአተኛ ሰው ከኃጢአቱ ሊነፃና ለኃጢአቱም ምህረት እንደሚያስፈልገው ሊሰማው ይገባል፡፡ ኃጢአተኛነቱም ተሰምቶት “አምላክ ሆይ እኔን ኃጢአተኛውን ማረኝ” (ሉቃስ 18፥13) እያለ ሊለምን ይገባዋል፡፡ ከኃጢአተኛነት አካሄዱ ተጸጽቶና በደለኛነቱን ተገንዝቦ አስቀድሞ ኃጢያቱን ለእግዚአብሔር መናዘዝ ሲኖርበት በመቀጠልም የበደላቸውን ሰዎች ይቅርታ መጠየቅና ለበደሉት ሁሉ ይቅርታ በማድረግ ከሰው ጋር ሰላምን ማውረድ ይገባዋል፡፡ የዓለምን ኃጢአት የሚስወግደውን የእግዚአብሔርን በግ (ዮሐ. 1፥29) በእምነት ቢመለከት ኢየሱስ ኃጢአቱን ሁሉ ይቅር ይለዋል፡፡

እግዚአብሔር ለኃጢአታችን ይቅርታ ማድረጉን በተለያዩ መንገዶች ይገልጻል፡፡ አንዳንዴ በቀላል አነጋገር “ኃጢአትህ ተሰረየችልህ” (ሉቃስ 5፥20) ይላል፡፡ ኃጢአታችን ይቅር ከተባለልን ከእግዚአብሔር ጋር ሰላም ይኖረናል፡፡ “እንግዲህ በእምነት ከጸደቅን በእግዚአብሔር ዘንድ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሰላምን እንያዝ” (ሮሜ 5፥1)፡፡ (በሌሎች ሰዎች ውሳኔ ስለተረጋገጠልን ወይም ስለተጠመቅን ወይም የቤተክርስቲያን አባል ስለሆንን ዳግመኛ ለመወለዳችን ማረጋገጫ ሊሆነን አይችልም፡፡) “ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር እልፎአል፤ እነሆ ሁሉም አዲስ ሆኖአል” (2ኛ ቆሮ. 5፥17)፡፡ ኢየሱስ ለኒቆዲሞስ በዮሐንስ ሶስት ላይ “እውነት እውነት እልሀለው፤ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም” ብሎ እንደነገረው በክርስቶስ የሆነ ሰው ሁሉ አዲስ ሆኖ ዳግም ተወልዷል፤ በመንፈስ መወለድ ማለትም እንዲህ ነው፡፡ የተፈጥሮ ልደት የተፈጥሮን ሕይወት ይሰጠናል፤ መንፈሳዊ ልደት ደግሞ መንፈሳዊ ሕይወትን ይሰጠናል፡፡ መንፈሳዊ ሕይወት ሊመጣ የሚችለው ሰው “ከውኃ (ከእግዚአብሔር ቃል) እና ከመንፈስ ሲወለድ ነው (ዮሐ. 3፥5)፡፡

ከመንፈስ የተወለደ ሰው ከሞት (መንፈሳዊ ሞት) ትንሳኤን በማግኘት “በላይ ያለውን የሚሻ” (ቈላ. 3፡1) ነው፡፡ “እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ቃሌን የሚሰማ የላከኝንም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፥ ከሞን ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም” (ዮሐ. 5፥24) ፡፡

የተሟላ መልዕክት ክፍል ለመዳናችን በግል ማስረገጫ

በስጋቸው ሀሳብ ሳይሆን በመንፈስ ለሚመሩና “በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን ኩነኔ የለባቸውም” (ሮሜ 8፡1)፡፡ እንዲህ አይነቶቹ ሰዎች ፍቅራቸው ያተኮረው በላይ ባለው እንጂ በምድራዊው ነገር አይደለም፤ በምድር ያሉ ብልቶቻቸውን የሚገድሉና በስጋ ሀሳብና ፈቃድ የማይመላለሱ ናቸው፡፡ “ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ፤ በዓለም ያለው ሁሉ እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት ስለ ገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም”  (1ኛ ዮሐ. 2፥15-16)፡፡ የእግዚአብሔር መንፈስ  “የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን ያ መንፈስ እራሱ ከመንፈሳችን ጋር ይመሰክራል፡፡ ልጆች ከሆንን ወራሾች ደግሞ ነን፤ ማለት የእግዚአብሔር ወራሾች ነን፤ አብረንም ደግሞ እንድንከበር አብረን መከራ ብንቀበል ከክርስቶስ ጋር አብረን ወራሾች” (ሮሜ 8፥16-17) እንደሆንን ያስረግጥልናል፡፡

“በተሰጠንም በመንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ፍቅር በልባችን” (ሮሜ 5፥5) ሲፈስ፤ ያኔ ወደ ሰማያዊ ነገሮች እንዘረጋለን፡፡ ቃሉን በማፍቀርና ይህንን ቃል በመመገብ ስለ ጌታችን እንድንመሰክር ይሆንልናል፡፡

ይህ ከእግዚአብሔር ዘንድ የሆነ ፍቅር ደግሞ ከተፈጥሯዊ ፍቅርና ከቤተሰባዊ ትስስር የበለጠ ነው፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ፍቅር ያለው ሁሉ ጠላቶቹን ይወዳል፤ የሚጠሉትንም እንዲያፈቅር ያስችለዋል (ማቴ. 5፡44)፡፡

ጌታ ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱን ሲልካቸው “እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው” (ማቴ. 28፥19-20) ብሎ አስተምሯቸዋል፡፡  

የተለወጡና ዳግመኛ የተወለዱ ክርስቲያኖች በመንፈሱ ሕያው በሆነና ከእግዚአብሔር በተጠራ አገልጋይ የውሃ ጥምቀት ተጠምቀው የእግዚአብሔርን ቤተክርስቲያን ይቀላቀላሉ፡፡ ከዚያም ክርስትናው በጸሎት የተሞላ ሕይወት ይሆናል፡፡ ጸሎት ለክርስቲያን አስፈላጊ እስትንፋሱ ነው፡፡ “በጌታና በኃይኩ ችሎት” (ኤፌ. 6፥10) የበረታ እንዲሆን መንፈሳዊ አቅሙና እና ወኔው በጸሎት ይታደሳል፤ በዚህም “ማንም አክሊልህን እንዳይወስድብህ ያለህን አጽንተህ ያዝ” (ራእይ 3፡11) የሚለውን ለመተግበር ያስችለናል፡፡  

ለተጨማሪ መረጃ ያግኙን

በረሪ የውንጌል ጽሑፎችን (ትራክቶችን) ለማዘዝ

ከሞት በኋላስ?

በአሁኑ ወቅት ሕያው ነዎት፤ ይተነፍሳሉ፤ ከቦታ ቦታ ይንቀሳቀሳሉ፤ ስራዎንም ያከናውናሉ፡፡ እየኖሩ ያሉት ሕይወት በምቾት ወይም በችግር የተሞላ ሕይወት ይሆናል፡፡ ፀሀይ ትወጣለች ደግሞም ትጠልቃለች፤ በአንድ ስፍራ ህጻን ይወለዳል በሌላ ስፍራ ደግሞ አንዱ ይሞታል፡፡

ሕይወት በአጠቃላይ ጊዜያዊ ቅንብር ነች፡፡

ነገር ግን

እርስዎ ከሞቱ በኋላ ወዴት ይሄዳሉ?

ኃይማኖተኛ ሰው ቢሆኑ፤ ወይም

ምንም አይነት ኃይማኖት ባይኖርዎ

ይህንን መሰረታዊ ጥያቄ መመለስ

ይኖርብዎታል፡፡ ምክንያቱም ሰው

ሁሉ ከአጭር የምድራዊ ቆይታው

በኋላ ወደ ዘላለም መኖሪያው

ያመራልና (መክብብ 12፡5)፡፡

ግን ወዴት?

የሚቀበሩበት የመቃብር ስፍራ ነፍሶን ማስቀረት አይቻለውም፡፡ በድንዎ በእሳት ተቃጥሎ ቢጠፋ፤ ነፍስዎን እሳት አይበላትም፡፡ በጥልቁ ባህር ውስት ገብተው ቢጠፉ፤ ነፍስዎ አትሰምጥም፡፡

ነፍስዎ በፍጹም አትሞትም!

የሰማይ እና የምድር ሁሉ አምላክ

የተሟላ መልዕክት ክፍል ከሞት በኋላስ?

“ነፍስ ሁሉ የኔ ናት” ብሎአል፡፡

ከዚህ ሕይወት በኋላ እውነተኛ ማንነትዎ የሆነችው ነፍስዎ፤ በሕይወት በምድር ላይ በነበሩበት ወቅት ከሰሯቸው መልካምም ይሁን ክፉ ስራዎት ጋር ትገናኛለች፡፡ ዕብራውያን 9፡27ን መልከቱ፡፡

ከልብዎ የሚያመልኩ ሰው ይሆኑ ይሆናል

ስለሚሰርዋቸው ያለተገቡ ተግባራት ይጸጸቱ ይሆናል

የሰረቁትን መልሰው ይሆናል

እነዚህ ሁሉ የሚያስፈልጉ ነገሮች ቢሆኑም

ስለ ኃጢአትዎ በራስዎ ስርየትን ማምጣት አይችሉም

በምድር ሁሉ ላይ ፈራጅ የሆነው የሰማይ አምላክ እግዚአብሔር ከፊቱ የተሰወረ አንዳች ነገር ስለሌለ የእርስዎን ኃጢአት እና ሕይወት በአጠቃላይ ያውቃል፡፡ እርስዎ ከነኃጢአትዎ ከሆኑ ሊመጣ ካለው ከእግዚአብሔር ክብርና ባርኮት ሊካፈሉ አይችሉም፡፡

ነገር ግን የኸው የሰማይ አምላክ የፍቅር አምላክ ነው፡፡ ለሕወትዎና ለነብስዎ የመዳኛ መንገድ ስላዘጋጀ የዘላለም ጥፋት ወደ ሆነው ወደ ገሃነም እሳት መጣል የለብዎትም፡፡ እግዚአብሔር ኢየሱስን ወደዚህ ምድር የላከው የእርስዎን ነብስ ለማዳን ነው፡፡ ኢየሱስ በቀላንዮ መስቀል ላይ ተሰቃይቶ ሲሞት የእርስዎ ኃጢአት ሁሉ በእርሱ ላይ ሆንዋል፡፡ እግዚአብሔር ሰማይ ሊያቀርብ የሚችለውን ድንቁን መስዋዕት ስለ እርስዎ ኃጢአት ሲል ሰጥትዋል፡፡ “እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን” (ኢሳይያስ 53፥5)፡፡ እነዚህ የትንቢት ቃላት የተነገሩት ኢየሱስ ወደ ምድር ከመምጣቱ ከብዙ ዘመናት በፊት ነው፡፡

ኢየሱስ እንደሚወድዎ ያምናሉ? ወደ እርሱ በመጸለይ ኃጢአትዎን ይናዘዛሉ? ንስሀ በመግባት የእግዚአብሔር ልጅ በሆነው በኢየሱስ ያምናሉ? በፍጹም መሰጠት ወደ እርሱ ከመጡ ለነብስዎ ሰላምን እንዲሁም ከሞት በኋላ የከበረ ሕይወትን ይሰጥዎታል፡፡ በሀሴት የተሞላ የዘላለም ቤትና የነብስ ሰላም እንዳልዎት እርግጠኛ መሆን የሚችሉት ይህንን ወሳኔ ሲወስኑ ብቻ ነው፡፡

ግን’ኮ አዳኝ የሆነውን የኢየሱስን ፍቅር በሕይወት ዘመናቸው ላልተቀበሉ ሁሉ የጥፋት ጉድጓድና ማብቂያ የሌለው የዘልለም እሳት ይጠብቃቸዋል፡፡ ከሞት በኋላ ወደ ኋላ መመለስና የመዳን ተስፋ ሁሉ ያበቃለታል፡፡

“በዚያን ጊዜ በግራው ያሉትን ደግሞ ይላቸዋል። እናንተ ርጉማን፥ ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱ” (ማቴ. 25፥41)፡፡ “የማይጠቅመውንም ባሪያ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል” (ማቴ. 25፥30)፡፡  

እግዚአብሔር፤ በመጽሐፍ ቅዱስ፤ በምድር ሁሉ ላይ ሊመጣ ስላለው የመጨረሻ ፍርድ አስጠንቅቋል፡፡ በእነዚህ ቅዱሳት መጻሕፍት ይህ የፍርድ ቀን ከመምጠቱ በፊት ግልጽና ተጨባጭ ምልክቶች እንደሚሆኑ ተጽፍዋል፡፡

ከመምጣቱ በፊት ጦርነትና የጦርነት ወሬ በየቦታው ይሰማል፤ ሕዝብ በሕዝብ ላይ ተነስቶ እርስ በእርስ አለመግባባት እና መፋጀት ይሆናል፤ መንግስታትም በመካከላቸው የሚነሳውን የሀሳብ ልዩነት እና አለመግባባት መፍታት ያቅታቸዋል፡፡

በተለያዩ ስፍራዎች የምድርም መናወጥና ቸነፈር ይሆናል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ በዚህ ወቅት ክፉዎች በክፋታቸው እየባሱ እንደሚሄዱ ይነግረናል፡፡ ብዙዎችም የእግዚአብሔርን ማስጠንቀቂያ ቸል በማለት ከእግዚአብሔር ይልቅ ተድላን የሚወዱ ይሆናሉ፡፡ በዘመናችን እነዚህን ትንቢቶቸ ሲፈጸሙ እያየን አይደለምን? ማቴዎስ 24፥6-7፤12 እና 2ኛ ጢሞቴዎስ 3፥4ን ይመልከቱ፡፡

አንድ ቀን ሁላችንም ለፈጸምናቸው ድርጊቶች ሁሉ ልንዳኝ ከፈጣሪያችን እና ጌታችን ፍርድ ወንበር ፊት እንቆማለን (ማቴዎስ 25፥32-33)፡፡ ጻድቅና ታላቅ ፈራጅ የሆነው አምላካችን በብልጽግናችን በድህነታችን፤ በእውቅናችን በመዋረዳች፤ በቆዳችን ቀለም፤ በዘራችን ላይ ያለተመሰረተ ጻድቅ ፍርድ እነደሚያስተላልፍ መዘንጋት የለብንም፡፡ 

ማብቂያ በሌለው ዘላለም ውስጥ የሰዓት መቁጠሪያና ዓመታዊ ቀን መቁጠሪያ (ካላንደር) አይኖሩም፤ ዘመናቱም መጨረሻቸው አይታወቅም፡፡ የኃጢአተኞችና እግዚአብሔርን ያልፈሩቱ የስቃያቸው ጭስ ለዘላለም በገሀነም ሲጬስ፤ የዳኑቱ ደስታ ዝማሬ በረከትና መጽናናት ማብቂያ በሌለው በእግዚአብሔር መንግስት ውስጥ ያስተጋባል፡፡ ምርጫዎን አሁኑኑ ይወስኑ፤ ምክንያቱም ይህ እድል በቅጽበት ከእጅዎ ሊወጣ ይችላልና፡፡ “እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ፥ የመዳን ቀን አሁን ነው” (2ቆሮንጦስ 6፥2) ፤ ማቴዎስ 11፥28፡፡

ለተጨማሪ መረጃ ያግኙን

በረሪ የውንጌል ጽሑፎችን (ትራክቶችን) ለማዘዝ

የአእምሮ ሰላም በአስጨናቂው ዓለም

Peace

ሰላም፤ ለአገራችን፣ ለቤታችን በተለይም ለልባችንና ለአእምሮአችን ሰላም የት ይገኛል? በሰዎች ዘንድ የሰላም የጥም ጩኸት ለዘመናት ሲያስተጋባ ኖርዋል፤ በተለይም ዓለም ከጊዜ ወደ ጊዜ እንደ አውሎ ንፋስ እየተናወጠችና ለአስደንጋጭ ክስተቶች ተጋላጭ እየሆነች በመጣች ቁጥር የሰላም ጉጉት ጩኸት ጎልቶ ይሰማል፡፡ ያንተስ የልብህ ጥማት ይሄ ነው? አለመርካትና ሁከት በነገሰበት ዓለም ውስጥ ሁሉን የሚያስንቅ ውስጣዊ ፀጥታን ማግኘት ትፈልጋለህ?

ዓለምን ለኑሮ ተስማሚ እና የተሻለች ለማድረግ የታለመ መጨረሻ የሌለው የስልጣኔ ጉዞ ህይወትን የባሰ ውስብስብ እንዲሆን አድርጎታል፡፡ ምንም እንኳን  ሰዎች በብዙ መልኩ ነገሮች ከወላጆቻቸው የተሻሉ ቢሆኑላቸውም እነርሱ ራሳቸው ግን የተሻሉ አይደሉም፡፡ ሰዎች በድካምና በስጋት ወስጥ ናቸው፡፡ ሰዎች ምሪት እና አማካሪ፣ ጥበቃ እና ዋስትና እንደሚያስፈልጋቸው አጠያያቂ አይደለም፡፡ ሁላችንም የአእምሮ ሠላም እንዲኖረን እንፈልጋለን፡፡

የአእምሮ ሰላም እንዴት ያለ ትልቅ ሀብት ነው! ይህን አይነት ሠላም ግጭትና ተስፋ መቁረጥ፣ አመፃና ችግር በበዛበት ዓለም ውስጥ ማግኘት  ይቻል ይሆን?

የተሟላ መልዕክት ክፍል የአእምሮ ሰላም በአስጨናቂው ዓለም

ታላቁ ፍለጋ ቀጥሏል! ብዙዎች ዝናንና ገንዘብ በማካበት፣ በተድላና በስልጣን፣ በትምህርትና በእውቀት ብዛት እና ትዳር በመመስረት ሰላምን ለማግኘት ይሞክራሉ፡፡ አእምሮአቸውን በእውቀት መሙላት እና ሀብት ማካበትን ይፈልጋሉ፤ ነፍሳቸው ግን ባዶ እንደሆነች ትቀራለች፡፡ ሌሎች በአደንዛዥ እፅ እና በአልኮል የህይወትን ገሃድ (እውነታ) ከመጋፈጥ ለመሸሽ ይሞክራሉ ነገር ግን የሚፈልጉትን ሰላም አያገኙትም፡፡ ፍለጋቸው ሁሉ መውጫ ወደሌለው ተስፋ አስቆራጭና ከንቱነት እሽክርክሮሽ ውስጥ ያስገባቸዋል፡፡ በአስጨናቂው ዓለም ውስጥ ብዙዎች አሁንም በባዶነትና በብቸኝነት አእምሮአቸው እየተጨነቀ ይኖራሉ፡፡

ብዙዎች ውጫዊ ከሆነውና ከሚጨበጠው ነገር ሰላምን ለማግኘት ይጣጣራሉ፤ ወደ ውስጣቸው መመልከትን ግን ቸል ብለዋል፡፡ በውስጣቸው ሊገኝ የሚችለውን  ይፈራሉና፡፡ ስለሚጨነቅ አእምሮአቸው አስጨናቂውን ዓለም ይኮንናሉ፡፡ ፈውስ ግን መጀመር ያለበት ከውስጥ ልባቸው ነው፡፡

ሰው በውጥረት ውስጥ

እግዚአብሔር ሰውን ከፈጠረው በኋላ በፍፁም ሰላም፣ ደስታ እና ተድላ መኖር እንዲችል ባማረ የአትክልት ስፍራ አስቀመጠው፡፡ ነገር ግን አዳምና ሄዋን የእግዚአብሔርን ትእዛዝ በተላለፉባት ሰአት ጸጸት ተሰማቸው ፡፡ በፊት የእግዚአብሔርን መገኘት ይናፍቁ ነበር፤ በኋላ ግን በሀፍረት እራሳቸውን ደበቁ፡፡ ያውቁት የነበረው ሰላምና ደስታ በጸጸትና እና በፍራቻ ተተካ፡፡ የዓለም ብሎም የአእምሮ ጭንቀት የጀመረው እዚህ ጋር ነበር፡፡

እንደ አዳምና ሄዋን አንተም ከእግዚአብሔር ሀሳብ ውጪ ስትሆን ህይወትህ በፍራቻና በጭንቀት ይሞላል፡፡ በኑሮህ እርግጠኛ ስላልሆንክባቸው ነገሮች፣ እየተለዋወጠ እና እያከተመለት ባለው ዓለም ላይ አስኩሮትህን ስታደርግ ሀሳብህን የጣልክበት እና የዋስትናህ መሰረት ይናጋል፡፡ ሰላም አይኖርህም ትረበሻለህ፡፡

ኃጢአት ሰውን ከእግዚአብሔር ለይቶታል፡፡”እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን” (ኢሳያስ 53፡6)፡፡ ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል (ሮሜ 3፡23)፡፡ ኃጢአት፣ ፍራቻ፣ ንዴት ራስ ወዳድነት እና ሌሎችም ጫና እያሳደሩበት ጠላት ሆነው ሰውን በሄደበት ሁሉ የሚከተሉት ቀንበር ሆነውበታል፡፡ እነዚህ መሰላቸትንና የአእምሮ ድካምን ያስከትላሉ፡፡

ራስ ወዳድነት ለሰው የመጀመሪያ አለመታዘዝ ስር መሰረት የጣለ ነበር፡፡ አሁንም ሰውን ወደ ተስፋ መቁረጥና ወደ ልብ ስብራት የሚገፋፋ መሰረታዊ ከሆኑ ክፉ ነገሮች አንዱ ነው፡፡ ለፍላጎቶችህና ለምኞቶችህ ራስወዳድ ከሆንክ  ስግብግብ  እና ጭንቀታም ያደርግሀል፡፡ በራስ ወዳድነትህ ብዙ ከቀጠልክ ጭንቀትህም እየጨመረ ይመጣል፡፡

እግዚአብሔርን ያማከለ ህይወት ሰላምን ይሰጣል

ራስህን የህልውናህ ማዕከል አድርገህ ከመመልከት ይልቅ ወደ እግዚአብሔር መለስ ብለህ እርሱን የህይወትህ አላማ ልታደርገው ያስፈልግሀል፡፡ እግዚአብሔር የህይወትህ ገዢ ካልሆነ ለጠባብ አስተሳሰብ፣ በራስ ለማዘን፣ ለፍራቻ እና ለጭንቀት በቀላሉ ተጋላጭ ትሆናለህ፡፡ መሪህ እግዚአብሔር ከሆነ ሕይወትህ በሁሉም አቅጣጫ የተሟላና በኑሮህም ደስተኛ ትሆናለህ፡፡ በእግዚአብሔር የምትመራ ልብ ብቻ በመረጋጋትና በሰላም ትኖራለች፡፡

መዝሙረኛው ዳዊት “ልቤ ጨካኝ ነው፥ አቤቱ፥ ልቤ ጨካኝ ነው፤ እቀኛለሁ፥ እዘምራለሁ” (መዝ. 57፡7) ብሎ ይናገራል፡፡ በሙሉ ልቡ እግዚአብሔርን በመታመኑ በአእምሮ እረፍት ሀሴት ማድረግ ችሏል፡፡ ልባችን በእግዚአብሔር ላይ ከተደገፈ በዙሪያችን አስጨናቂ ነገሮች ቢኖሩም ውስጣችን ግን ሰላም ይሆናል፡፡ “በሁሉ እንገፋለን እንጂ አንጨነቅም፤ እናመነታለን እንጂ ተስፋ አንቆርጥም” (2ቆሮ. 4፡8) እንደሚለው መሆን ይቻላል፡፡

ኢየሱስ ክርስቶስ የሰላም ምንጭ

ኢየሱስ ሰዎችን ሁሉ አላማ ወዳለው እና ማንነትን ወደ ሚለውጥ ህይወት ይጋብዛል፡፡ “እኔን መከተል የሚወድ ቢኖር፥ ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ” (ማቴ. 16፡24)፡፡ “ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል” (2ቆሮ. 5፡17)፡፡ “ወደ እኔ ኑ” የሚለውን የኢየሱስን ጥሪ ትቀበላለህ? በጨለማ ምትክ ብርሀንን፣ በግራመጋባት ፈንታ መታመንን፣ ለታወከ ሰላምን፣ ላዘነ ደስታን፣ ለደከመ እረፍትን፣ተስፋ ለቆረጠ ተስፋን እና ለሞተው ህይወትን መስጠት ይችላል፡፡  

እግዚአብሔር ሰውን ከአምላኳ ጋር መገናኘትን የምትጠማ ሕያው ነፍስ እንዲኖረው አድርጎ ፈጥሮታል፡፡ “ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደሚናፍቅ፥ አቤቱ፥ እንዲሁ ነፍሴ ወደ አንተ ትናፍቃለች። ነፍሴ ወደ ሕያው አምላክ ተጠማች፤ መቼ እደርሳለሁ? የአምላክንስ ፊት መቼ አያለሁ?” (መዝ. 42፡1-2)፡፡ ነፍስን ማርካት የሚችል ሕያው እግዚአብሔር ብቻ ነው፡፡ ይሄን እርግጠኛ መሆን ትችላለህ፤ ከእግዚአብሔር ጋር ካልተስማማህ በቀር መቼም እውነተኛ ሰላም ሊኖርህ አይችልም፡፡

በልባችን ያለው የውጊያ ሜዳ

ነፍሳችን አምላኳን ብትጠማም በሀጢአት የተሞላ ማንነታችን ግን በእግዚአብሔር ላይ ያምፃል፡፡ ከፊል ማንነታችን እግዚአብሔርን ይናፍቃል ከፊሉ ደግሞ ወደ ስጋ ምኞት ይሳባል፡፡ ልባችን የማያቋርጥ ትግል ያለበት የውጊያ ሜዳ ነው፡፡ ይህ ውስጣዊ ትግል ለውጥረትና ጭንቀት ምክኒያት ይሆናል፡፡ ያለ እግዚአብሔር “እንደሚንቀሳቀስ ባሕር ናቸው፤ ጸጥ ይል ዘንድ አይችልምና፥ ውኆቹም ጭቃና ጕድፍ ያወጣሉና ” (ኢሳ. 57፡20) እንደሚለው ነን፡፡

ህይወታችን ማለትም አእምሮአችን፣ አካላችን እና መንፈሳችን በፈጠረንና እና በሚያውቀን በአንዱ በእግዚአብሔር ካልተስተካከለ በስተቀር ዘላቂ ሰላም ሊኖረን አይችልም፡፡ እርሱ የአለማት ጌታ ብቻ ሳይሆን የእኔን እና ያንተን ሕይወት ከጅማሬው እስከ ፍፃሜውም የሚያውቅ ነው፡፡ ስለኛ በማሰብ ወደ አለም መጣ “ብርሃኑም በጨለማና በሞት ጥላ ተቀምጠው ላሉት ያበራል እግሮቻችንንም በሰላም መንገድ ያቀናል” (ሉቃስ 1፡79)፡፡

የሰላም አለቃ የሆነ ኢየሱስ ወደ እሱ እንድትመጣ ይጠይቅሀል “እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ ” (ማቴ. 11፡28)፡፡ ወደ እሱ ስትመጣ በሚሰጥህ ነፃነት እረፍትና እፎይታን ታገኛለህ፡፡ ሰላምህ እንደሚፈስ ወንዝ ይሆናል፤ “ሰላምህ እንደ ወንዝ ጽድቅህም እንደ ባሕር ሞገድ በሆነ ነበር፤ ” (ኢሳ. 48፡18)፡፡ ሸክምህን ሁሉ በእርሱ ላይ በማራገፍ ወደ ኢየሱስ ትመጣለህ? “ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ . . . ልባችሁ አይታወክ አይፍራም” (ዮሐ. 14፡27) ይልሀል፡፡

 

የፍርሀትና የስጋት መድሀኒት እምነት ነው፡፡ ከዘለአለም እስከ ዘለአለም የሚኖር፣ ከቶ የማይለወጥ ወዳጅ፣ ፍቅሩም የማያረጀውን እግዚአብሔርን መታመን እንዴት እረፍት ነው፡፡ ይህ ወዳጅ ሁሌም ያስብልናል፤ ይጠነቀቅልናል፡፡ ስለዚህ ለምን ሀሳብ ይግባን ለምንስ እንጨነቅ? በ 1ኛ ጴጥ. 5፡7 ላይ “እርሱ ስለ እናንተ ያስባልና የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት” የሚለውን መተግበርን ተለማመድ፡፡ ውጊያው ሲጠናቀቅ ሰላም አለ፤ ታዲያ ህይወትህን ለዚህ ጌታ ለምን አትሰጥም? አስታውስ፣ ካመንክ አትጨነቅም፤ ከተጨነክ አታምንም፡፡ “በአንተ ታምናለችና በአንተ ለምትደገፍ ነፍስ ፈጽመህ በሰላም ትጠብቃታለህ ” (ኢሳ. 26፡3)

ቅሬታ ወይም ንዴት የአእምሮህን ሰላም የሚሰርቅ መርዝ ነው፡፡ ወደ ተስፋ መቁረጥና ተስፋን ወደሚያጨልም ግራ መጋባት ይመራል፡፡ የበደሉህን ሰዎች ይቅርታ ለማድረግ ከባድ ሊሆን ይችላል፤ አንተ ይቅር መባል ከፈለክ ግን ይቅረታ ማድረግ ግዴታህ ነው፡፡ “ለሰዎች ግን ኃጢአታቸውን ይቅር ባትሉ፥ አባታችሁም ኃጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም” (ማቴ. 6፡15)፡፡ እምነት በልብህ ሲወለድ ፈቃድህን ለአምላክህ ማስገዛት አይከብድህም፡፡ ቂም ከመያዝና ከመበሳጨት ይልቅ ልብህ በፍቅርና በይቅርታ ይሞላል ከዚያ ውስጣዊ እርጋታን ታገኛለህ፡፡ ኢየሱስ የልብህ ገዢ ሲሆን ጠላቶችህን መውደድ ትችላለህ፡፡ የክርስቶስ ደም ነፃ ሲያወጣህ ብቻ ይህን ማድረግ ትችላለህ፡፡

ሀጢአትን መናዘዝ እና ንሰሀ መግባት የአእምሮ ሠላም ይሰጣል

ከዚህ በፊት የሰራሀቸው የሀጢአቶችህ ሸክም ከብዶህ መሸከም ከምትችለው በላይ እንደሆነ ተሰምቶህ ይሆናል፡፡ ጌታ ለከበደብህ ሸክም በ የሐዋ. ሥራ 3፡19 መፍትሄን ይሰጥሀል፡፡ “እንግዲህ ኃጢአታችሁ እንዲደመሰስ ንስሐ ግቡ፤ ከመንገዳችሁም ተመለሱ፤ በጌታም ዘንድ የመታደስ ዘመን ይመጣላችኋል(አ.መ.ት)”፡፡ (1ዮሐ. 1፡9) “በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው” ይላል፡፡ “እንግዲህ በእምነት ከጸደቅን በእግዚአብሔር ዘንድ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሰላምን እንያዝ” (ሮሜ 5፡1)፡፡

በመዝሙር 23 ላይ ዳዊት በእግዚያብሔር ላይ ያለውን እምነት ይገልፃል፡፡ በህይወቱ ስለተለማመደው ሰላም ሰፊ ማብራሪያ ይሰጣል፡፡ ሰላምና ህብረት ከእረኛው ጋር የጠበቀ ወዳጅነት ላላቸው ሁሉ ነው፡፡

መዝሙር ሀያ ሶስት

እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፥ የሚያሳጣኝም የለም።  በለመለመ መስክ ያሳድረኛል፤ በዕረፍት ውኃ ዘንድ ይመራኛል።  ነፍሴን መለሳት፥ ስለ ስሙም በጽድቅ መንገድ መራኝ። በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም፤ በትርህና ምርኵዝህ እነርሱ ያጸናኑኛል።  በፊቴ ገበታን አዘጋጀህልኝ በጠላቶቼ ፊት ለፊት ራሴን በዘይት ቀባህ፥ ጽዋዬም የተረፈ ነው። ቸርነትህና ምሕረትህ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ይከተሉኛል፥ በእግዚአሔርም ቤት ለዘላለም እኖራለሁ።

ይሄን እረኛ ታውቀዋለህ? በእርሱ አምነሀል፣ ተደግፈሀል? ኢሳያስ ይህ ሩሩህ እና መሀሪ እረኛ “መንጋውን እንደ እረኛ ያሰማራል፥ ጠቦቶቹን በክንዱ ሰብስቦ በብብቱ ይሸከማል” (ኢሳ. 40፡11) ይለናል፡፡ ከግራ መጋባት ለመውጣትና ዘላለማዊ እረፍረት ወዳለበት የእግዚአብሔር ክንድ ውስጥ ለመግባት ዝግጁ ነህ፡፡ ይለፈውን የሀጢአተኝነት ህይወትህን፣ እያለፍክበት ያለውን ፈተናህን፣ የወደፊት ስጋትህን እና ሙሉ ማንነትህን ለጌታ አሳልፈህ ልትሰጠው ተዘጋጅተሀል፡፡ ጌታ ምርጫውን ያቀርብልሀል፡፡ መወሰን የአንተ ድርሻ ነው፡፡

ዘላቂ ሠላም

በሙሉ ልብህ ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ስትመጣ የአእምሮ ሠላምን ለማግኘት የምታደርገው ፍለጋህ ያበቃል፡፡ እርሱን በማመን ብቻ የሚገኝን ሰላምና እረፍት ይሰጥሀል፡፡ እንደ ገጣሚው ለማለትም ትችላለህ፣

ሠላም በሌነበት፣ ሠላምን አውቃለሁ

ወጀብ ባንሰራራበት እርጋታ ያለበት

ሚስጥራዊ በሆነ ቦታ፣ ፊት ለፊት

ከጌታዬ ጋር ልሆን የምችልበት

ራልፍ ስፓልዲንግ ኩሽማን-

 

በአስጨናቂው ዓለም ሠላም ይኖርሀል! የልብህን በር ለክርስቶስ አሁን ክፈትለት፤ እርሱም አንድ ቀን ለዘላለም ፍፁም ዕረፍት ያለበት የመንግስተ ሰማይን በር ይከፍትልሀል፡፡

ለተጨማሪ መረጃ ያግኙን

በረሪ የውንጌል ጽሑፎችን (ትራክቶችን) ለማዘዝ