አድምጥ! የሚጠራህ ማን ነው?

The listening lamb

የዮሐንስ ወንጌል 10፡ 1-18

አንድ ሰው ሲጠራህና የሚጠራህ ሰው ድምጽ ከየት አቅጣጫ እንደሚመጣ ለማወቅ ግራ ተጋብተህ ታውቅ ይሆን? ወይም ብዙ ጫጫታ መካከል ከመሆንህ የተነሳ የሚጠራህን ሰው ድምጽ ለመስማት ተቸግረህ ታውቅ ይሆን?

አድምጥ! አንድ ድምጽ እየጠራህ ነው፡፡ አዎ አንተን!

የተሟላ መልዕክት ክፍል አድምጥ! የሚጠራህ ማን ነው?

አንተ ማን ነህ? ስምህ ማን ነው? ከየት ነው የመጣኸው? የት ነው ምትኖረው? ወዴትስ እየተጓዝክ ነው?

የምትኖርበትን አካባቢ ስም ታውቃለህ፡፡ ድነገትም ከምትኖርበት አካባቢ ርቀህ ተጉዘህ አታውቅ ይሆናል፡፡ ነገር ግን የምትኖርበት አካባቢ የአንድ አገር አካል፤ አገራት ደግሞ የአለም አካል እንደሆኑ ታውቃለህ;፡፡

መጽሐፍ ቅዱስ

አለማችን ከተፈጠረች 6,000 ዓመታት ሆንዋታል፡፡ የተፈጠረችውም በእግዚአብሔር ነው፡፡ እግዚአብሔር ዓለምንና የመጀመሪያውን ሰው እንዴት እንደፈጠረ የተረከበት መጽሐፍ ቅዱስ የተባለ መጽሐፍ አለው፡፡ እግዚአብሔር ሰውን የፈጠረው በአምሳሉ ነው፡፡

ከዚያን ግዜ ጀምሮ ብዙ ልጆች ተወልደዋል፡፡ ብዙ ሰውችም ሞተዋል፡፡

አንተ የተወለድከው ከአባትና እናትህ ነው፡፡ ነገር ግን የሰራህ እግዚአብሔር ነው፡፡ እርሱ አንተን ብቻ ሳይሆን ሁሉን ነገር የፈጠረ አምላክ ነው፡፡ እግዚአብሔር ሁሉን ነገር እንዴት አድርጎ እንደ ሰራ እና አንተን እንዴት አድርጎ እንደፈጠረ አስበህ ታውቅ ይሆን? 

ወላጆችህ ስም አውጥተውልሀል፡፡ እግዚአብሔር ስምህን ያውቃል፡፡ በማንኛውም ቋንቋ ቢሆን እግዚአብሔር የእያንዳንዱን ሰው ስም ያውቃል፡፡ እርሱ ሁሉን አዋቂ ነው፡፡

እግዚአብሔር ፈጣሪያችን ስለሆን ስለ እኛ ሁሉን ያውቃል፡፡ እኛ የእርሱ ስለሆንን ይወደናል፡፡ እርሱ ከአባትና እናታችን ይልቅ አብልጦ የሚጠነቀቅልን በሰማይ የሚኖር አባታችን ነው፡፡

እግዚአብሔር

እግዚአብሔር የነበረ፣ ያለ እና ለዘላለም የሚኖር አምላክ ነው፡፡ ስለዚህም እስትንፋሱን በሰጠን ጊዜ እኛንም ለዘላለም እንድንኖር አድርጎናል፡፡ ነገር ግን ስጋችን ሟች ስለሆነ እርሱ ሳይሆን ለዘላለም የሚኖረው በውስጣችን የምትኖር ነብሳችን ነች ዘላለማዊ፡፡

እግዚአብሔርን ታውቀዋለህ? ድንገት “እግዚአብሔር ማን ነው? የትስ ነው የሚኖረው?” ብለህ ትጠይቅ ይሆናል፡፡

በእርግጥ ማወቅ ትፈልጋለህ? አዎ! በርግጥም ማወቅ ትፈልጋለህ፡፡ ውስጥህ በርግጥም ማወቅ ይፈልጋል፡፡

እግዚአብሔርን አይተኸው አታውቅም፤ ታውቃለህ እንዴ? አላየኸውም ማለት እኮ ታዲያ እግዚአብሔር የለም ማለት አይደለም፡፡

አንድ እግዚአብሔር ብቻ ነው ያለው፡፡ ከርሱ በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ ምክንያቱም እውነተኛ አምላክ በሰማይና በምድር የሚኖር አምላክ ነው፡፡ እርሱ በአንድ ጊዜ በሁሉም ቦታ ይገኛል፡፡

የእግዚአብሔር መኖሪያ የተዋበውና በላይ ያለው ሰማይ ነው፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር ድምጹን በሚታዘዙ ሰዎች ልብም ውስጥ ይኖራል፡፡

“እግዚአብሔርን ለማወቅ እንዴት መማር እችላለሁ?” የሚለውን ጥያቄ ትጠይቅ ይሆን? እግዚአብሔር እንዴት ልናውቀው እንደምንችል ድንቅ መንገድን አዘጋጅቶልናል፡፡

እግዚአብሔር ማን እንደሆነ እና ምን እንደሚመስል ለሰዎች ሁሉ እንዲያሳይ አንድያ ልጁ የሆነውን ኢየሱስን ከሰማይ ልኮታል፡፡ አብና ወልድ አንድ ናቸው፡፡

የእግዚአብሔር ልጅ በተአምራት ህጻን ልጅ ሆኖ ተወለደ፤ ትልቅም ሰው ሆኖ አደገ፡፡ ኢየሱስ ካደገ በኋላ ለሶስት ዓመታት ስለአባቱ ፍቅር ለሰዎች አስተማረ፡፡ ጨምሮም እግዚአብሔር ቅዱስ እንደሆነና ኃጢአትን እንደሚጸየፍ አስተማረ፡፡

ከዛም እግዚአብሔር ከኃጢአታችን የምንድንበትን መንገድ አዘጋጀልን፡፡ ልጁ ኢየሱስ በክፉዎች እጅ ወድቆ መስቀል ላይ እንዲሰቀል ፈቀደ፡፡ ኢየሱስ ከታላቅ ፍቅሩ የተነሳ ሕይወቱን ስለ እኛ አሳልፎ ሰጠ!

ኢየሱስ የዓለምን ሁሉ የኃጢአት ዋጋ ሊከፍል የቻለ መስዋዕት ነበር፡፡ አንተ ለሰራኸው ኃጢአት ሁሉ፤ ለትልቅ ለትንሹ፤ ለወንድ ለሴቱ ኃጢአት ሁሉ መስዋዕት የሆነው ኢየሱስ ነው፡፡

ኢየሱስ በመስቀል ላይ እንደተሰቀለ ቀረን? በመቃብርስ ተቀብሮ ቀረ? በፍጹም፣ ከሶስት ቀን በኋላ በድል ተነስቶ ወደ ሰማይ አረገ፡፡ የዚህች ዓለም ፍጻሜ በሚሆንበት ጊዜ የሰው ሁሉ ጻድቅ ፈራጅ ሆኖ ይገለጣል፡፡

የዮሐንስ ወንጌል ካለህ ምዕራፍ አስርን (10) አንብብ፡፡ ዮሐንስ ኢየሱስ ለህዝቡ ምን ያስተምራቸው እንደነበር ነው የጻፈው፡፡ ኢየሱስ ያን ጊዜ ለህዝቡ ያስተማረው ትምህር ዛሬ ለእኛም ትምህርት ነው፡፡ ኢየሱስ መልካም እረኛ እንደሆነ እና ነፍሱንም ስለ በጎቹ አሳልፎ እንደሰጠ ተናግርዋል፡፡ በጎቹ ደግሞ እኛ ነን፡፡ በጎቹ የሆኑት ድምጹን ያውቃሉ፡፡ እያንዳንዳቸውን በስም ይጠራቸዋል፤ እነሱም ሌላውን ከመከተል ይሸሻሉ፡፡

እንግዳው፤ ሌላኛው ድምጽ

እንግዳ የተባለው እና ልንሸሸው የሚገባው ማንን ነው? ኦ! ሌባውን ነው፡፡ እርሱ ስለ በጎቹ ምንም ደንታ የለውም፡፡ ውሸታም ስለሆነ አንዳች እውነት በእርሱ ዘንድ የለም፡፡ እርሱ ዲያብሎስ ነው፤ እርሱ ጠላታችን የሆነው ሰይጣን ነው፡፡

አስቀድሞ እርሱ የእግዚአብሔር ጠላት ነው፡፡ በአንድ ወቅት ከእግዚአብሔር ጋር በሰማይ ይኖር የነበረ ቅዱስ መልአክ ነበር፡፡ ነገር ግን በትዕቢት እራሱን ከእግዚአብሔር በላይ ከፍ ሊያደርግ ሞከረ፡፡ ከእግዚአብሔር ጋር ተዋጋ፣ ብዙ መላእክትም ተባበሩት፡፡ እግዚአብሔር ኃያል ስለሆነ ድል በመንሳት ሰይጣንን ከነተከታዮቹ ከገነት አባረራቸው፡፡ ከዚህም የተነሳ ሰይጣንን እግዚአብሔርን ይጠላዋል፡፡

ሰይጣን እግዚአብሔር አጠገብ መቅረብ ስለማይችል እግዚአብሔር በአምሳሉ በፈጠራቸው ሰዎች ላይ ተቆጣ፡፡ ሰይጣን ኃጢአተኛ ስለሆነ ሰው ሁሉ ኃጢአት እንዲሰራ ያባብላል፡፡ ኃጢአት ዳግመኛ ወደ ገነት ሊገባ ፈጽሞ አይችልም፡፡

እግዚአብሔር ለዲያብሎስ እና መላእክቱ ሁሉ የሰራው ሌላ ስፍራ አለ፡፡ ይህ ስፍራ ሲኦል ነው፡፡ ሲኦል እሳቱ የማይጠፋ  የስቃይ ቦታ ነው፡፡ ዲያብሎስ እና ተከታዮቹ ሁሉ ለዘላለም የሚቀጡበት ቦታ ነው፡፡ እኛም የሰይጣንን ድምጽ ለመስማት የምንመርጥ ከሆነ እግዚአብሔር ወደዚህ ቦታ ይልከናል፡፡

ሰይጣን ስለ ሲኦልም ሆን ስለ እግዚአብሔር እንድናስብ አይፈልግም፡፡ ስለ እግዚአብሔር እንድናስብ ስለማይፈልግ ስለ እግዚአብሔር የሆኑ ሀሳቦቻችንን ሁሉ በመስረቅ የእርሱን ድምጽ እንድንሰማ ሊያደርገን ይሞክራል፡፡

በውስጥህ ያን የተለየውን የእንግዳውን ድምጽ ሰምተህ ታውቃለህ?

ሰይጣን አንዳንዴ መልካም ነገር እንደሚሰጠን አድርጎ ያሳምነናል፡፡ አንዳንድ ጊዜ “እኔ ከሌሎች የተሻልኩ ነኝ፤ እኔ ከማንም በላይ አስፈላጊ ሰው ነኝ፤ ቅድሚያ ለእኔ ነው የሚገባው፤ አለቀውም/አለቃትም፤ ለመብቴ መታገል አለብኝ፤ በቂ ስለማላገኝ ብሰርቅም ችግር የለውም፤ ሁሉ ስለሚዋሹ እኔም ብዋሽ ችግር የለውም፤ ምን እያሰብኩ እንደሆነ ማንም ስለማያውቅ ጸያፍ ሀሳቦችን ባስብ ምንም ችግር የለውም፤ በብልግና የተሞሉ ቃላት በጣም ስለሚያስቁ ምንም ችግር የለባቸውም” ብለን እንድናስብ ያደርገናል፡፡

በሌላ ጊዜ ደግሞ ተስፋ አስቆርጦን “የማልረባ ነኝ፤ በሕይወት መኖሬ ምንም ትርጉም የለውም” ብለን እንድናስብ ያደርጋል፡፡

እነዚህ ሁሉ የዲያብሎስ ድምጾች ናቸው፡፡ እርሱ ውሸታም ነው፤ እኛንም ውሸታሞች ሊያደርገን የሚጥረው ለዚህ ነው፡፡ እርሱ ሌባ ነው፤ እኛም እንድንሰርቅ የሚፈልገው ለዚህ ነው፡፡ እርሱ ነፍሰ ገዳይ ነው፤ እኛም ሌሎችን የምንጠላ ሰዎች ሊያደርገን የሚጥረው ለዚህ ነው፡፡

ይህንን አይነቱን ድምጽ ስትሰማ ምን ዓይነት ስሜት ይሰማሀል? ውስጥህን ደስ ያሰኝህ ይሆን? ኦ! በፍጹም ደስታ እንዳይሰማህ ያደርጋል፡፡ መደበቅ እንድትፈልግ ያደርግሀል፡፡ ሰይጣንም ልክ እንደዚህ ነው፤ ነገሮችን በጨለማ ተደብቆ ማድረግ ነው የሚወደው፡፡

ኢየሱስ፤ የእረኛው ድምጽ

መልካሙን እረኛ ኢየሱስን ታውቀዋለህን? የእርሱ በግ መሆን ትፈልጋለህን? ድምጹን ማወቅ ትፈልጋለህን?

አዎ ትችላለህ፡፡ ነገር ግን በመጀመሪያ ያንን ሌላኛውን ድምጽ መስማት ማቆም አለብህ፡፡

በጸጥታ ውስጥ ሆነህ ስታዳምጥ ኢየሱስ ዝግ ባለ ድምጽ ሕይወትህን አሳልፈህ እንድትሰጠው ጥሪን ሲያቀርብልህ ትሰማዋለህ፡፡ ኃጢአትህን ሁሉ ተናዘህ ንስሀ እንድትገባ ሲነግርህ ትሰማዋለህ፡፡    

አንዳንድ ጊዜ ተረጋግተህ ተቀምጠህ ሳለ “ችግሮቼን እና ሸክሞቼን ምን ላድርጋቸው? መልካም ሰው ብሆን እመኛለሁ፤ የማልታመምበት ወይም የማልራብበት ቦታ ብኖር ማናለ፤ ስሞት ምን እሆናለሁ?” የሚሉ ሀሳቦች አስበህ ሊሆን ይችላል፡፡

ድንገት ከእነዚህ የበለጡ ብዙ ሀሳቦች አስበህ ሊሆን ይችላል፡፡ ይህ ድምጽ ኢየሱስ አንተን እየተጠራ ያለበት ድምጽ ነው፡፡

አንዳንድ ጊዜ ምክንያቱን ሳታውቀው የሀዘን ስሜት ይሰማህ ይሆን? ወይም ሰው አብሮህ እያለ የብቸኝነት ስሜት ይሰማህ ይሆን? ይህ የሚሆንበት ምክንያት የፈጠረህና ሚወድህ እግዚአብሔር አብሮህ ስላልሆነ ሊሆን ይችላል፡፡ እርሱ የጠፉትን በጎቹን የሚፈልግ እረኛ ነው፡፡ ደጋግሞ እየጠራህ እና እየፈለገህ ነው!

የእረኛውን ድምጽ ስትሰማ መልስን ስጠው፡፡ ከኃጢአትህ ነጻ መውጣት እንደምትፈልግ ንገረው፡፡ የሚሰማህን ንገረው፤ እንዲያድንህም ጠይቀው፡፡ ጸሎት ማለት እንደዚህ ነው፡፡

ወደ ሰማይ አምላክ እግዚአብሔር ጸልየህ ታውቅ ይሆን? አሁኑኑ ጸልይ፡፡ እርሱ ይሰማሀለ፤ ይረዳህማል፡፡ ዘወትር የምትናፍቀውን ሰላም ይሰጥሀል፡፡

የእርሱ በግ በመሆን ድምጹን ማወቅ ትፈልጋለህ? እርሱ ወዳጅህ ሊሆንህ እና ከኃጢአት ሸክምህ ሊያሳርፍህ ይፈልጋል፡፡ ያን ጊዜ ውስጥህ በደስታ ይሞላል፤ እንደ እርሱም አፍቃሪ እና ቸር ትሆናለህ፡፡ ፍራቻዎችህን ሁሉ ድል እንድትነሳ ይረዳሀል፡፡

ሌሎች ክርስቲያን በመሆንህ ቢያሾፉብህም አንተ ግን ኢየሱስ እንደሚጠነቀቅልህ ትረዳለህ፡፡ እንግዳው እየመጣ ቢፈትንህም ኢየሱስ እንድታሸንፈው እንደሚረዳህ ልታምነው ይገባል፡፡

በእረኛው የፍቅር እቅፍ ውስጥ ስታርፍ፣ እርሱ በመጨረሻ ድንቅ ወደ ሆነውና በደስታ ወደ ተሞላው ቤቱ ከእግዚአብሔር ጋር ለዘላለም እንድትኖር እንደሚወስድህ ትረዳለህ

ለተጨማሪ መረጃ ያግኙን

በረሪ የውንጌል ጽሑፎችን (ትራክቶችን) ለማዘዝ