ልናቀው የሚገባ ከሁሉ የበለጠ ታሪክ

Bible and Candle

በመጀመሪያ አለማችን ባዶ ነበረች፡፡

አሶች በባህር፣

ከዋክብት በሰማይ ላይ አልነበሩም፤

የተሟላ መልዕክት ክፍል ልናቀው የሚገባ ከሁሉ የበለጠ ታሪክ

ባህርና ውብ አበቦች የሉም ነበር፡፡

ነገር ግን እግዚአብሔር ነበር፡፡

እግዚአብሔር አስደናቂ እቅድ ነበረው፡፡ ውብ የሆነች አለምን ለመስራት አሰበ፡፡ እንዳሰበም ፈጠራት፡፡ እግዚአብሔር አለምን ሲፈጥር ከምንም ነው የሰራት፡፡ “…..ይሁን” አለ፤ ሆነም!

ብርሀንን ፈጠረ፡፡ ወንዞችንና ባህርን፣ በሳር የተሸፈነች ምድርን፣ እንስሳትን፣ አእዋፋትንና ዛፎችን ሁሉ ሰራ፡፡

በመጨረሻ ሰውን ፈጠረ፡፡ ለፈጠረው ሰውም ሚስትን አበጀለት፡፡ ስማቸውም አዳምና ሔዋን ይባል ነበር፡፡

እግዚአብሐር አዳምና ሔዋንን በጣም ይወዳቸው ነበር፡፡ ይኖሩበት በነበረበት በውቡ ገነት ሁልግዜ አመሻሹ ላይ እየመጣ ያነጋግራቸው ነበር፡፡

አዳምና ሔዋን እግዚአብሔር ከከለከላቸው ከአንድ ዛፍ በስተቀር ከገነት ዛፍ ሁሉ እንዲበሉ ተፈቅዶላቸው ነበር፡፡

አዳምና ሔዋን የእግዚአብሔር ጠላት የሆነው ሰይጣን እስከፈተናቸው ቀን ድረስ በደስታ በገነት ይኖሩ ነበር፡፡ ነገር ግን አንድ ቀን እግዚአብሔር እንዳይበሉ ከከለከላቸው ዛፍ ፍሬ ለመብላት ወሰኑ፡፡ በዚህም ኃጢአትን ሰሩ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ሀፍረትና ሀዘን ገባቸው፡፡

ከዚያን ጊዜ በኋላ ከእግዚአብሔር ጋር እንደ ቀድሞው መነጋገር አልቻሉም፡፡ ያንን ፍሬ ከበሉ በኋላ መከራና ችግር ሊደርስባቸውና ሞትን ሊሞቱ ሆነ፡፡ በሰሩት ስህተት እንዴት ያለ ሀዘንን አዝነው ይሆን!

እግዚአብሔር ሊረዳቸው ቃል ገባላቸው፡፡ የተወሰነው ጊዜ ሲደርስ ልጁን ኢየሱስን ወደ አለም እንደሚልክና ኢየሱስም ከሰማይ ወርዶ ኃጢአት ይቅር እንዲባል መንገድን እንደሚያበጅ ነበር ተስፋን የሰጠው፡፡ የኃጢአት ይቅርታ እንዲሆን ኢየሱስ ለሰው ሁሉ መከራን መቀበልና መሞት ነበረበት፡፡ አዳምና ሔዋን እግዚአብሔር አዳኝን እንደሚልክላቸው ሲያውቁ እንዴት ያለ ታላቅ ደስታ ተሰምቷቸው ይሆን!

አዳምና ሔዋን ልጆችንና የልጅ ልጆችን ወለዱ፡፡ ቀስ በቀስም ብዙ ሰዎች በዚች ምድር ላይ መኖር ጀመሩ፡፡

እግዚአብሔር ሁሉ ሰው ደስተኛ እንዲሆን ይፈልግ ነበር፡፡ ምን ማድረግ እንዳለባቸው ነገራቸው፡፡ እግዚአብሔር እንዲያደርጉት የሰጣቸው ህግጋት ዝርዝር የሚከተለው ነው፡-

  1. ከእኔ በቀር ሌሎች አማልክት አይሁኑልህ፡፡
  2. የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ፡፡
  3. የእግዚአብሔርን የአምላክህን ስም በከንቱ አትጥራ፡፡
  4. የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ አስብ፡፡
  5. አባትህንና እናትህን አክብር፡፡
  6. አትግደል፡፡
  7. አታመንዝር፡፡
  8. አትስረቅ፡፡
  9. በባልንጀራህ ላይ በሐሰት አትመስክር፡፡
  10. የባልንጀራህን ቤት አትመኝ የባልንጀራህን ሚስት ሎሌውንም ገረዱንም በሬውንም አህያውንም ከባልንጀራህ ገንዘብ ሁሉ ማናቸውንም አትመኝ፡፡ (ዘጸአት 20፥3-17)

እነዚህን ህግጋት እኛም ማንበብ እንድንችል በመጽሐፍ ቅዱስ ተጽፈውልናል፡፡ ከታዘዝናቸውና ካደረግናቸው ደስተኞች እንሆናለን፡፡

ሰይጣን እነዚህን ህግጋት እንድንታዘዝ አይፈልግም፡፡ አንዳንዴ፣ በተለይም ደግሞ ሰው በማያየን ቦታ እንድንሰርቅ ይነግረናል፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር ሁሉን የሚያይ አምላክ ስለሆነ የምናደረገውን ሁሉ ያውቃል፡፡

ሰይጣን አንዳንድ ግዜ ውሸትን እንድንዋሽና የዋሸነውን ውሸት ማንም እንደማያውቅብን እንድናስብ ያደርገናል፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር ሁሉን የሚሰማ አምላክ ስለሆነ የምንለውን ሁሉ ያውቃል፡፡

አንዲህ ያሉ ኃጢአት ስንሰራ ውስጣችንን ሰላም አይሰማንም፡፡ እግዚአብሔር ስለሚወደን መልካም ሰዎች እንድንሆን ሊረዳን ይፈልጋል፡፡ ኢየሱስን ወደ አለም የላከውም ለዚህ ነው፡፡ የገባውን ተስፋ ፈጽሞ አልረሳም፡፡

ከብዙ አመታት በኋላ ኢየሱስ እንደ ሕጻን ተወለደ፡፡ አድጎም ሙሉ ሰው ሆነ፡፡

ብዙ አስደናቂ ነገሮችን አደረገ፡፡ ሕሙማን ፈወሰ፣ እውራንን አበራ፣ ሕጻናትን ባረከ፡፡

ኢየሱስ ምንም በደል አልሰራም ነበር፡፡ ይልቁንም ለሰዎች ስለ እግዚአብሔርና እንዴት ሊታዘዙት እንደሚገባ አስተማራቸው፡፡

ከጥቂት ጊዜ በኋላ የኢየሱስ ጠላቶች ኢየሱስን በመስቀል ሰቅለው ገደሉት፡፡

ኢየሱስ መከራን ተቀብሎ የሞተው ለሰው ልጆች ሁሉ ኃጢአት ሲሆን፤ ይህ መስዋዕቱ የሰቀሉትንም ሰዎች ኃጢአት ያካትት ነበር፡፡

ኢየሱስ ከሞቱ በኋላ ተቀበረ፡፡ ነገር ግን ከዛን በኋላ አስደናቂ ነገር ሆነ፡፡ ኢየሱስ እንደተቀበረ አልቀረም፤ ከሙታን ተነሳ፡፡

ከትንሳኤው ጥቂት ጊዜ በኋላ እግዚአብሔር ኢየሱስን በደመና ወደ ሰማይ ወሰደው፡፡ መላዕክት ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲያርግ ቆመው ሲመለከቱ ለነበሩ ደቀ መዛሙርቱ ተመልሶ እንደሚመጣ ነገሯቸው፡፡

ኢየሱስ የሞተው ለእኛም ኃጢአት ጭምር ነው፡፡ ኃጢአታችንን ተጸጽተን እንድንናዘዝና ንስሀ እንድነገባ ይፈልጋል፡፡ ይህንን ብናደርግ ይቅርታን ሊሰጠን ዝግጁ ነው፡፡

በማንኛውም ግዜ ወደ እግዚአብሔር መጸለይ ትችላለህ፡፡ እርሱ እያንዳንዷን ቃላችንን የሚሰማና ሀሳባችንን ሁሉ የሚያውቅ አምላክ ነው፡፡ ኃጢአታችን ይቅር ሲባልልን በውስጣችን ደስታ እንዲሰማን ያደርጋል፡፡ ከዛም መልካም የሆነውን ሁሉ ለማድግ የምንፈልግ ሰዎች እንሆናለን፡፡

እግዚአብሔርን አለመታዘዝና ሰይጣንን መከተል እንመርጥ ይሆናል፡፡ ነገር ግን የእግዚአብሔር ቃል በዚህ ዓለም በምኖርበት ጊዜ ለእግዚአብሔር ጥሪ ምላሻችን እምቢታ ከሆነ ወደ ገሀነም እንደምንጣል ይነግረናል፡፡ ገሀነም ለዘላለም ሲነድ የሚኖር እሳት ነው፡፡

ነገር ግን ኢየሱስን ብንወደውና ብንታዘዘው ወደ ምድር መጥቶ በሚመለስበት ጊዜ ወደ ሰማይ ይዞን ይሄዳል፡፡ መንግስተ ሰማይ የእግዚአብሔርና የልጁ የኢየሱስ ውብ መኖሪያ ነው፡፡ የፍቅርና የብርሀን ቤት ነው፡፡ በእዚያ ለዘላለም በደስታ እንኖራለን፡፡

ለተጨማሪ መረጃ ያግኙን

በረሪ የውንጌል ጽሑፎችን (ትራክቶችን) ለማዘዝ