የአንተ ወዳጅ

Jesus is your friend

ኢየሱስ የአንተ ወዳጅ

እኔ አንድ ወዳጅ አለኝ፡፡ እርሱ ከወዳጆቼ ሁሉ ይልቅ የቅርብ ወዳጄ ነው፡፡ እርሱ በጣም ደግና እውነተኛ ስለሆነ አንተም እንድትተዋወቀው እፈልጋለሁ፡፡ ስሙ ኢየሱስ ይባላል፡፡ እርሱ የአንተም ወዳጅ መሆን ስለሚፈልግ በጣም ድንቅ ነገር ነው፡፡

ስለ እርሱ ልንገርህ፡፡ የእርሱን ታሪክ ከመጽሐፍ ቅዱስ እናነባለን፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ እውነትና የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡

የተሟላ መልዕክት ክፍል የአንተ ወዳጅ

አለምና በአለም ውስጥ ያለውን ሁሉ የፈጠረ እግዚአብሔር ነው፡፡ እርሱ የሰማይና የምድር አምላክ ነው፡፡ እርሱ ሕይወትንና እስትንፋስን ለሁሉም ይሰጣል፡፡

God's creation

ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው፡፡ ኢየሱስ የግል አዳኛችን እንዲሆን እግዚአብሔር ከሰማይ ላከው፡፡ እግዚአብሔር ዓለሙን በጣም ስለወደደ (ያ ማለት አንተንና እኔን ወደደ ማለት ነው) አንድያ ልጁ የሆነው ኢየሱስን ለኃጢአታችን እንዲሞትና የሚያምንበት ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ ወደ አለም ላከው (ዮሐንስ 3፥16)፡፡

ኢየሱስ ወደ ምድር እንደ ትንሽ ሕጻን ልጅ መጣ፡፡ በምድር ላይ በነበረበት ወቅት አባትና እናቱ ዮሴፍና ማርያም ነበሩ፡፡ እርሱ በጋጣ ተወልዶና በግርግም ተኝቶ ነበር፡፡

Jesus' birth

ኢየሱስ ከዮሴፍና ማርያም ጋር አድጓልና ታዘዛቸው፡፡ አብሯቸው የሚጫወታቸው ወንድሞችና እህቶች ነበሩት፡፡ ዮሴፍንም በአናጺነት ስራው ያግዘው ነበር፡፡

Jesus and the lad with food

ኢየሱስ ትልቅ ሰው ሲሆን ሰዎችን ስለ ሰማይ አባቱ አስተማራቸው፡፡ እግዚአብሔር እንደሚወዳቸው አሳያቸው፡፡ ሕመምተኞችን ፈወሰ፤ በችግር ወስጥ የነበሩትንም ሁሉ አጽናና፡፡ ኢየሱስ የልጆች ወዳጅ ነበር፡፡ ልጆች ወደ እርሱ እንዲቀርቡ ፈለገ፡፡ ለእንርሱም ጊዜ ሰጣቸው፡፡ ልጆች ኢየሱስን ወደዱት፤ ከእርሱም ጋር አብረው ጊዜ ማሳለፍን ይወዱ ነበር፡፡ 
አንዳንድ ሰዎች ኢየሱስን አልወደዱትም፡፡ ተመቀኙትና ጠሉት፡፡ በጣም ስለጠሉትም ሊገድሉት ፈለጉ፡፡ አንድ አሰቃቂ ቀን ኢየሱስን በመስቀል ሰቅለው ገደሉት፡፡ ኢየሱስ ምንም በደል አልሰራም ነበር፡፡ አንተና እኔ ስለ በደልን እርሱ በቦታችን ሞተ፡፡

Jesus on the cross

የኢየሱስ ታሪክ በሞቱ አያበቃም፡፡ እግዚአብሔር ከሞት አስነሳው! ተከታዮቹም አዩት፡፡ ከዛም አንድ ቀን ወደ ሰማይ ተመለሰ፡፡
ዛሬ እርሱ ሊያይህና ሊሰማህ ይችላል፡፡ እርሱ ስላንተ ሁሉን ያውቃል፤ ይጠብቅህማል፡፡ በጸሎት ወደ እርሱ ና፡፡

Jesus listening to a woman pray

 

 

ለተጨማሪ መረጃ ያግኙን

በረሪ የውንጌል ጽሑፎችን (ትራክቶችን) ለማዘዝ

ክፍሊቱ

ክፍሊቱ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ሙታንንም ታናናሾችንና ታላላቆችን በዙፋኑ ፊት ቆመው አየሁ፥ መጻሕፍትም ተከፈቱ፤ ሌላ መጽሐፍም ተከፈተ እርሱም የሕይወት መጽሐፍ ነው፤ ሙታንም በመጻሕፍት ተጽፎ እንደ ነበረ እንደ ሥራቸው መጠን ተከፈሉ” (ራእይ 20፥12) የሚል ጥቅስን እናነባለን፤ ይህም እግዚአብሔር የእያንዳንዳችንን ሕይወት መዝግቦ እንደሚያስቀምት ማስረጃ ነው፡፡ 

በአሜሪካን አገር ሜሪላንድ ከተማ ነዋሪ የሆነው ጆሽዋ ሄሪስ የተባለ አንድ ወጣት የተወሰነ ጊዜን ለማሳለፍ ፖርቶሪኮ የተባለች ሀገር ነበር፡፡  በዚች ሀገር በነበረው ቆይታም አንድ ምሽት ሕልምን አለመ፡፡ ይህ ወጣት እግዚአብሔር ይህን ህልም ያሳየው ታማኝነት ከጎደለው የሕይወት ጉዞው እንዲመለስ ሊገስጸው እንደሆን ተሰማው፡፡ በዛን ምሽት ያየው ሕልም ሕይወት መቀየር የሚችለውን የኢየሱስ ክርስቶስን ኃይል እና የደሙን ጉልበት አስታውሶታል፡፡ እኛም ይህ ወጣት ያየውን ሕልም ልናካፍልህ እንወዳለን፡፡

(ክፍሊቱ)

በእንቅልፍ ሰመመን ውስጥ ሆኜ እራሴን በአንዲት ክፍል ውስጥ አገኘሁት፡፡ በዚህች ክፍል ውስጥ አንደኛውን የክፍልዋን ግድግዳ ከሸፈነው ትንንሽ የስምና የአድራሻ ማውጫ አይነት ካርዶችን የያዙ ማህደሮች ከተደረደሩበት መደርደሪያ በስተቀር ምንም የተለየ ነገር አልነበረም፡፡ እነዚህ ማህደሮች በቤተ መጽሐፍት ውስጥ ደራሲን ወይም የመጽሐፍን ርዕስ ተጠቅመን መጽሐፍ እንደመናወጣባቸው ካርዶች በፊደል ቅደም ተከተል የተደረደሩ ነበር፡፡ እነዚህ ማህደሮች ከወለሉ አንስተው እስከ ጣራው ድረስ ተደርድረው በሁለቱም አቅጣጫ መጨረሻ የሌላቸው ይመስሉ የነበር ሲሆን ሁሉም ማህደሮች የተለያዩ ርዕሶችን ይዘው ነበር የተደረደሩት፡፡ ማህደሮቹ ወደ ተደረደሩበት ግድግዳ እየተጠጋሁ ስመጣ “የወደድኳቸው ልጃገረዶች” የሚል ርዕስ ያለው ማህደር ቀልቤን ሳበው፡፡ ይህን ርዕስ የያዘውን ማህደር በመግለጥ ካርዶቹ ላይ የተጻፉትን ማንበብ ጀመርኩ፡፡ በካርዶቹ ላይ ተጽፈው የነበሩትን ስሞች አውቃቸው ስለነበር ደንግጬ በፍጥነት ማህደሩን ዘጋሁት፡፡

ከዛም ማንም ምንም ሳይነግረኝ የት እንደምገን ተገነዘብኩ፡፡ ይህቺ ማህደሮች የታጨቁባት ሕይወት አልባ ክፍል የእኔም ሕይወት ተመዝግቦ የተቀመጠባት ‘ማህደር ክፍል’ እንደሆነች ተረዳሁ፡፡ በዚህች ክፍል ውስጥ ላስታውሳቸው ከምችላቸው በላይ ትልቁም ይሁን ትንሹ እያንዳንዱ የሕይወት ክንዋኔዎቼ ተመዝግበው ተቀምጠዋል፡፡

አለፍ አለፍ እያልኩ የተለያዩ ማህደሮችን እያነሳሁ በውስጣቸው ተጽፎ የሰፈረውን ማንበብ ስጀምር መገረምና ጉጉት ከፍርሀት ጋር ውስጤን ሲወረኝ ተሰማኝ፡፡ ከማነባቸው ነገሮች አንዳንዶቹ ደስታን እና ጣፋጭ ትዝታን ሲያጭሩብኝ ሌሎች ግን ወደ ኋላዬ በመዞር ከበስተጀርባዬ የሚያየኝ ሰው ያለ እስኪመስለኝ ድረስ ሀፍረት እና ጸጸትን ይጭሩብኝ ነበር፡፡ “ወዳጆች” የሚል ማህደር “የከዳኋቸው ወዳጆች” ከሚል ማህደር አጠገብ ተቀምጦ ነበር፡፡

የተሟላ መልዕክት ክፍል ክፍሊቱ

ማህደሮቹ ካደረኳቸው ተራ ነገሮች አንስቶ እስከ ተገለጡ ትልልቅ ክፋቶቼ ድረስ በተለያየ ርዕስ ተመዝግበው ተቀምጠው ነበር፡፡ “ያነበብኳቸው መጽሐፍት”፣ “የተናገርኳቸው ውሸቶች”፣ “ለሌሎች ሰዎች ያደረኳቸው ማጽናናቶች”፣ “የሳቅሁባቸው ቀልዶች” የሚሉ ሁሉ ይገኙ ነበር፡፡  “ወንድሞቼ ላይ የጮህኳቸው ነገሮች” የሚል ርዕስ ያለው አይነት ማህደሮችን ስመለከት የርዕሶቹ ትክክለኛነት በራሱ ያስቀኝ ነበር፡፡ እንደ “ቤተሰቦቼ ላይ ያኩተመተምኳቸው ነገሮች” አይነት ርዕስ ያላቸው ማህደሮች ደግሞ ምንም የማያስቁ ነበሩ፡፡ የተለያዩ ካርዶችን ባነበብኩበት ጊዜ ሁሉ ካርዶቹ ላይ ተጽፈው በነበሩት ዝርዝር ይዘቶች መደነቄን አላቆምኩም ነበር፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ከጠበኳቸው በላይ ካርዶች በአንድ ማህደር ውስጥ የነበሩ ሲሆን አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ተስፋ ካደረኳቸው ካርዶች ያነሱ ካርዶች ነበሩ፡፡

እነዚህን ማህደሮች ማየቴ ይህን ሁሉ ነገር አድርጊያለሁ ወይ ብዬ እንድገረም አድርጎኛል፡፡ በሀያ አመታት እድሜዬ እነዚህን በሺዎች ምናልባትም በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ካርዶችን ለመጻፍ የሚያስችል በቂ ጊዜ ነበረኝን? እያንዳንዱ ያየሁት ካርድ ግን ጊዜ እንደነበረኝ የሚያስረግጥ ነበር፤ ምክንያቱም እያንዳንዱ ካርድ በራሴ የእጅ ጽሁፍ የተጻፈ እና የራሴው ፊርማ ያረፈበት ነበር፡፡

“የሰማኋቸው ዘፈኖች” የሚል ርዕስ ያለበትን ዶሴ አውጥቼ ስመለከት የዶሴው ይዘት እየጨመረ ሲሄድ ይታወቀኝ ነበር፡፡ ካርዶቹ በጣም ተጠጋግተውና ተጠቅጥቀው ተቀምጠው የነበረ ሲሆን ከሁለትና ሶስት ሜትር በኋላ እንኳን የማህደሩውን መጨረሻ ማግኘት አልቻልኩም ነበር፡፡ እነዚህን ሁሉ ሙዚቃዎች ለማዳመጥ ባባከንኩት ጊዜ አፍሬ ማህደሩን ዘጋሁት፡፡

“የዝሙት ምኞት” የሚል ርዕስ ያለው ማህደር ጋር ስደርስ ሰውነቴን ሲቀዘቅዘኝ ተሰማኝ፡፡ የማህደሩን ትልቀት ላለማየት በትንሹ ሳብ አደረኩትና አንድ ካርድ ከውስጡ አወጣሁ፡፡ በላዩ ላይ ሰፍሮ የነበረውን ዝርዝር ይዘት ሳነብ በፍርሀት ተንቀጠቀጥኩ፡፡ እንዲህ አይነት አሳፋሪ ጊዜ ተመዝግቦ በመቀመጡ ሕመም ተሰማኝ፡፡

ድንገት ኃይለኛ ቁጣ በውስጤ ሲቀሰቀስ ታወቀኝ፡፡ “እነዚህን ካርዶች ማንም ማየት የለበትም! ማጥፋት አለብኝ!” የሚለው ሀሳብ ተቆጣጠረኝ፡፡ እንደ እብድ አድርጎኝ ማህደሩን ጎትቼ አወጣሁት፡፡ ምንም ትልቅ ቢሆንም አስብ የነበረው በውስጡ ያሉትን ካርዶች አራግፎ ማቃጠል ነበር፡፡ ነገር ግን ካርዶቹን ከማህደሩ ውስጥ አውጥቼ ወለሉ ላይ ለማራገፍ ስሞክር አንድም ካርድ ማውጣት አልቻልኩም፡፡ ካርዶቹን በእጄ በመያዝ ለመቀዳደድ ብሞክርም እንደ ብረት ጠንካራ የሆኑ በመሆናቸው ማንም ላደርግ አልቻልኩም፡፡

ተሸንፌ እና ተስፋ ቆርጬ ማህደሩን ወደ ነበረበት ቦታ መለስኩት፡፡ ግንባሬን ግድግዳው ላይ አስደግፌ በራሴ በማዘን በረጅሙ ተነፈስኩ፡፡ ድንገት ወደ ማህደሮቹ ስመለከት “ወንጌልን የሰበኩላቸው ሰዎች” የሚል ርዕስ የያዘ ማህደር አየሁ፡፡ የዚህ ማህደር እጀታ በአጠገቡ ካሉ ማህደሮች ደመቅ ያለ ሲሆን ምንም ያለተነካ በመሆኑ አዲስ ነበር፡፡ ይህን ማህደር ይዤ ስስበው ርዝመትዋ ከስምንት ሴንቲ ሜትር ያልበለጠች ትንሽዬ ሳጥን እጄ ላይ ወደቀች፡፡ በውስጥዋ የነበረው ካርድ ብዛት በአንድ እጄ ልቆጥረው የምችለው ነበር፡፡

ከዛም እንባ በአይኔ ላይ ግጥም አለና ማልቀስ ጀመርኩ፡፡ በጉልበቴ ተንበርክኬ ከሆዴ ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩ፡፡ አለቅስ የነበረው ከተሰማኝ ታላቅ የሀፍረት ስሜት የተነሳ ነበር፡፡ እንባ ያዘሉ አይኖቼ በማህደሮች የተሞላውን መደርደሪያ ተመለከቱት፡፡ ስለዚህ ክፍል ማንም ሰው በፍጹም ማወቅ የለበትም፤ ቆልፌ ቁልፉን መደበቅ አለብን ብዬ አሰብኩ፡፡

እንባዬን ከአይኔ እየጠራረኩ እያለ ድንገት አየሁት፡፡ ወይኔ፣ በፍጹም እሱ መሆን የለበትም፡፡ እዚህ ቦታ ካልጠፋ ሰው ኢየሱስ ይገኛል ብዬ ያየሁትን ማማን አቃተኝ፡፡

ማህደሮቹን እየከፈተ ካርዶቹን ሲያነብ በተስፋ መቁረጥ እመለከተው ነበር፡፡ ምን ይለኝ ይሆን የሚለውን ሳስብ ከአቅሜ በላይ ሆነብኝ፡፡ ቀና ብዬ ፊቱን አተኩሬ ለማየት አቅም አጣሁ፡፡ ነገር ግን ከኔ በላይ ሀዘን እንደተሰማው ያስታውቅ ነበር፡፡ ሆን ብሎ መጥፎ መጥፎ የተመዘገበባቸውን ማህደሮች እያወጣ የሚያነብ መሰለኝ፡፡ እያንዳንዱን ነገር የሚያነበው ለምንድን ነው?

በመጨረሻ ዞር ብሎ በሀዘን ስሜት ተመለከተኝ፡፡ አስተያየቱ ንዴትን ሳይሆን ራሴን ዝቅ አድርጌ፣ ፊቴን በእጄ ሸፍኜ ድጋሚ ማልቀስ እንድጀምር አደረገኝ፡፡ ወደ እኔ መጣና በእጆቹ ትከሻዬ ላይ አቀፈኝ፡፡ ብዙ ብዙ ነገሮችን ማለት ሲችል ምንም ሳይናገር አብሮኝ አለቀሰ፡፡

ከዛም ብድግ ብሎ ወደ ማህደሮቹ ሄደ፡፡ ከአንዱ ጥግ ጀምሮ ማህደሮቹን እየመዘዘና እያንዳንዱን ካርድ እያወጣ የእኔን ስም እየሰረዘ በስሙ መተካት ጀመረ፡፡

“በፍጹም አይሆንም!” ብዬ በመጮህ በፍጥነት ቆሞ ወደ ነበረበት ቦታ ሄድኩ፡፡ ይዞት የነበረውን ካርድ ተቀብዬው በወቅቱ ማለት የቻልኩትን “በፍጹም አይሆንም” የሚለውን ቃል ደጋግሜ አልኩት፡፡ ስሙ በእነዚህ ካርዶች ላይ በፍጹም መጻፍ የለበትም ብዬ አሰብኩ፡፡ ነገር ግን በደማቅና የሚያምር ቀይ ቀለም የእኔ ስም ጠፍቶ የእርሱ ስም ተተካ፡፡ በደሙ ነበር የተጻፈው፡፡

በእርጋታ ካርዱን ከተቀበለኝ በኋላ በሀዘን የተሞላ ፈገግታን ፈገግ ብሎ ካርዶቹ ላይ ስሜን በስሙ መተካትና መፈረሙን ቀጠለ፡፡ እንዴት እንደሆነ በፍጹም ልረዳው ባልቻልኩት ፍጥነት የመጨረሻውን ካርድ ፈርሞ ማህደሩን በቦታው አስቀምጦ አጠገቤ መጥቶ ሲቆም አየሁት፡፡ እጁን ትከሻዬ ላይ አድርጎ “ተፈጸመ” አለ፡፡

ተንስቼ ቆምኩና እየመራኝ ከክፍሊቱ ወጣን፡፡ በክፍሊቱ በር ላይ ምንም ቁልፍ አልነበረም፡፡ ነገር ግን ገና የሚጻፍባቸው ብዙ ባዶ ካርዶች ነበሩ፡፡

*****

እግዚአብሔር ሕይወትህን እንዴት እንደሚመለከተው አስበህ ታውቅ ይሆን? “እኔ እላችኋለሁ፥ ሰዎች ስለሚናገሩት ስለ ከንቱ ነገር ሁሉ በፍርድ ቀን መልስ ይሰጡበታል” (ማቴዎስ 12፥36)፡፡ ለራሳችን ታማኞች ብንሆንና ባንዋሽ ደጋግመን በሀሳባችን እና በድርጊቶቻችን ኃጢአት መስራታችንን በሀዘንና በጸጸት እናምናለን፡፡ እኛም በሚስጥር ስላሰላሰልናቸው ሀሳቦች እና ስለሰራናቸው ስራዎች ማፈራችን አይቀርም፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ በሮሜ 2፥16 ላይ “እግዚአብሔር በኢየሱስ ክርስቶስ……..በሰው ዘንድ የተሰወረውን በሚፈርድበት ቀን ይሆናል” ይላል፡፡ ሐዋርያው ጴጥሮስ “እንግዲህ ከጌታ ፊት የመጽናናት ዘመን እንድትመጣላችሁ……..ኃጢአታችሁ ይደመሰስ ዘንድ ንስሐ ግቡ ተመለሱም” (የሐዋርያት ሥራ 3፥19) ብሎ ሰብኳል፡፡ ኃጢአትህ በኢየሱስ ተደምስሶለሀል ነው ወይንስ ዛሬም ያሳድድሀል?

ነጻ መውጣት ትፈልጋለህን? ያለፈው ሕይወት ዘመንህ የሀሳብ እና የድርጊት ኃጢአት ሸክም ከብዶብሀልን? ኃጢአቶቻችን የልባችን እና የሕይወታችን ከባድ ሸክም ናቸው፡፡ “ኃጢአት የለብንም ብንል ራሳችንን እናስታለን፥ እውነትም በእኛ ውስጥ የለም” (1ኛ ዮሐንስ 1፥8)፡፡ “የኃጢአት ደመወዝ ሞት ነውና፤ የእግዚአብሔር የጸጋ ስጦታ ግን በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን የዘላለም ሕይወት ነው” (ሮሜ 6፥23)።

ኢየሱስ ዛሬም ምህረትን ያደርጋል፡፡ ወደ አለም የመጣውና ደሙን ያፈሰሰው ለኃጢአተኞች ሁሉ ነው፡፡ እግዚአብሔር አቅዶት የነበረው የመዳን መንገድ ተገልጥዋል፡፡ መዳን ትወዳለህን? “እንግዲህ ልጁ አርነት ቢያወጣችሁ በእውነት አርነት ትወጣላችሁ” (ዮሐንስ 8፥36) ፤ (መዝሙር 51)። ወደ ኢየሱስ አሁን ና! ተጸጽተህ ኃጢአትህን ሁሉ ተናዘዝ፡፡ “በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው” (1ኛ ዮሐንስ 1፥9)። ኢየሱስ ከእርሱ ጋር እርካታ ወደ ሞላበት ሕይወት እንደሚመራህ እመነው፡፡ በእለት ተእለት የሕይወት እርምጃህ ምሪትን ይሰጥሀል፡፡ 

ክፍሊቱ - የባለቤትነት መብት 1995

New Attitudes/ Joshua Harris.

ለተጨማሪ መረጃ ያግኙን

በረሪ የውንጌል ጽሑፎችን (ትራክቶችን) ለማዘዝ

የጌታ የመምጫው ጊዜ ቀርቧል

ሌባ ሳይታሰብ በሌሊት እንደሚመጣ ጌታም እንዲሁ በድንገት ይመጣል (2ኛ ጴጥሮስ 3፡19)፡፡ የጌታ የመምጫ ጊዜ ቅርብ እንደሆነ ለምን እናምናለን? በዙሪያህ እየሆነ ያለውን ስትመለከት፤ ምን ያሳስብሀል?

መጽሀፍ ቅዱስ በመጨረሻው ዘመን ምን እንደሚሆን ይነግረናል፡፡ የተነገረውም እያንዳንዱ ነገር እየተፈፀመ ነው፡፡ “በዚያች ወራት ከጥፋት ውኃ በፊት፥ ኖኅ ወደ መርከብ እስከገባበት ቀን ድረስ፥ ሲበሉና ሲጠጡ ሲያገቡና ሲጋቡም እንደ ነበሩ፥ የጥፋት ውኃም መጥቶ ሁሉን እስከ ወሰደ ድረስ እንዳላወቁ፥ የሰው ልጅ መምጣት ደግሞ እንዲሁ ይሆናል” (ማቴዎስ 24፡38-39)፡፡ እግዚአብሔር የመጀመሪያውን ዓለም ሰው ራስ ወዳድና የልቡም ሀሳብ ክፉ ስለነበረ በውሀ አጠፋው፡፡ ዓለም በአመፃ የተሞላች ነበረች፡፡ እነሱም “ከእግዚአብሔር ይልቅ ተድላን የሚወዱ ” (2ኛ ጢሞቴዎስ 3፡4) ነበሩ፡፡ ዛሬም ሰዎች ከመቼውም ይልቅ ተድላን የሚወዱ ሆነዋል፤ ተድላን ለማግኘትም የተቻላቸውን ሁሉ ያደርጋሉ፡፡

ዓለም ያለችበትን ሁኔታ እስኪ እንመልከት፡፡ ክፋት እና ጥላቻ በብዙ ከተሞች ላይ አይሏል፡፡ ደም መፋሰስና ግድያ እለታዊ ክስተቶች ሆነዋል፡፡ ለምን? ሰዎች እግዚአብሔርን ረስተዋል፡፡ ወጣቶች ቀዥቃዦችና ያልተረጋጉ ሆነዋል? እናትና አባት ልጆቻቸው የቅርብ ክትትል በሚያስፈልጋቸው ወቅት ትተዋቸው ከቤት ርቀው ሄደው  ይሰራሉ፡፡ ወደ ጎዳኖች በመውጣት ለብዙ ችግሮች ተጋላጭ ይሆናሉ፡፡ በወጣትነት እድሜያቸው የሚቀጩ ሰዎች ቁጥር ከአመት አመት እየጨመረ መጥቷል፡፡ ወንጀል ከቀላል ደረጃ ወደ አስከፊ ደረጃ ደርሶአል፡፡ ምን ታስባለህ፤ ነገሮች የሚሻሻሉ ይመስልሀል? ለውጥ የሚታይበት ነገር ተመልክተሀል? ይህ ሁኔታ እስከመቼ ይቀጥል ይሆን? እግዚአብሔር ታጋሽ ነው ነገርግን መንፈሱ ሁሌም ከሰው ጋር ሲታገል አይኖርም፡፡ ሰዎች ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት ስለ ስራቸው መልስ የሚሰጡበት የቁርጥ ቀን ይመጣል፡፡  

የዛሬ ጊዜ ክርስቲያንስ እንዴት ነው? ቅድሚያ መስጠት ላለበት ነገር ቅድሚያን የሚሰጥ ነው? ወይስ ዓለማዊ  ነገሮች አጨናግፈውት እውነተኛ ብርሃኑን እንዳያበራ አግደውታል? የምድር ጨው የማዳን ሀይሉን አጥቶ ይሆን? መጽሀፍ ቅዱስ በእናንተ ያለው ብርሃን ጨልሞ ከሆነ ጨለማው እንዴት ከፍቷል ይለናል፡፡ አዎን ሁላችንም ብርሃኑ እንደበዘዘ ማስተዋል እንዳለብን አምናለሁ፤ ነፍሳትም ሁሉ በታላቁ ፈራጅ ፊት ቆመው ስለ ስራቸው ምላሽ የሚሰጡበት ቀን ቅርብ ነው፡፡

መጽሀፍ ቅዱስ በግልጽ እንደሚለን ኢየሱስ ይመጣል፡፡ “ይህንም ከተናገረ በኋላ እነርሱ እያዩት ከፍ ከፍ አለ፤ ደመናም ከዓይናቸው ሰውራ ተቀበለችው እርሱም ሲሄድ ወደ ሰማይ ትኵር ብለው ሲመለከቱ ሳሉ፥ እነሆ፥ ነጫጭ ልብስ የለበሱ ሁለት ሰዎች በአጠገባቸው ቆሙ፤ደግሞም የገሊላ ሰዎች ሆይ፥ ወደስማይ እየተመለከታችሁ ስለ ምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል አሉአቸው” (የሐዋ. ስራ 1፡9-11)፡፡ ወዳጄ ሆይ፤ ይህ ክስተት ሲሆን አያመልጠንም፡፡ አይን ሁሉ ሲመጣ ያዩታል፡፡ ጌታ ይመጣል፤ ሲመጣም “አሕዛብም ሁሉ በፊቱ ይሰበሰባሉ፤ እረኛም በጎቹን ከፍየሎች እንደሚለይ እርስ በርሳቸው ይለያቸዋል” (ማቴዎስ 25፡32)፡፡ የተወሰኑት ከእርሱ ጋር ወደ ክብር ይሄዳሉ ሌሎች ይቀራሉ፡፡ አንተስ አብረህ ወደ ክብር ትሄዳለህ ወይስ ወደ ኋላ ትቀራለህ? መምረጥ አለብህ፡፡

እኛ ሁላችን ሀጢአተኞች ነን

የተሟላ መልዕክት ክፍል የጌታ የመምጫው ጊዜ ቀርቧል

ሁላችንም ሀጢአትን የሚሰራ ተፈጥሮ አለን፤ ለሀጢአት ባሮች ነን፡፡ እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ተፍተናል፡፡ መልካም የሚያደርግ የለም አንድስ አንኳ፡፡ ማንም ከሀጢአት የነፃሁኝ ነኝ ሊል አይችልም፡፡ መዋሸት፣ ማታለልና መስረቅ የሰው ተፈጥሮው ነው፡፡ ከልጅነታችን ትክክል እንዳልሆኑ እያወቅን የምናደርጋቸው ብዙ ነገሮች አሉ፡፡ ወደ አዋቂነት እድሜ መጥተንም እነዛኑ ነገሮች ለማድረግ እንደምንፈልግ አውቀናል፡፡ ሀጢአት ደመዎዝ አለው፡፡ ዋጋውን ሳይቀበል አይቀርም “በገዛ ሥጋው የሚዘራ ከሥጋ መበስበስን ያጭዳልና” (ገላትያ 6፡8)፡፡ ለሀጢአታችን ብዛት የሚገባውን ካሳ መክፈል የምንችልበት አቅም የለንም፤ ሀጢአትም ከቶ ወደ መንግስተ ሰማይ ሊገባ አይችልም፡፡ ስለዚህ ምን ይበጀናል? ንሰሀ ካልገባን  በስተቀር ተስፋ በሌለበት እንቀራለን፡፡  

አንድ ቀን ጌታ የተዘጋጁትን፣ ዳግም የተወለዱትን ከእርሱ ጋር በክብር እንዲሆኑ ሊወስዳቸው ከሰማይ ይወርዳል (1ኛ ተሰሎንቄ 4፡16-17)፡፡ መንግስተ ሰማይ ያማረና አስደሳች ይሆናል፡፡ “ነገር ግን። ዓይን ያላየችው ጆሮም ያልሰማው በሰውም ልብ ያልታሰበው እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀው” (1ኛ ቆሮንጦስ 2፡9)፡፡ ዝግጁዎች ካልሆንን ወደ ኋላ እንቀራለን፡፡ መጽሀፍ ቅዱስ፣ ከዚያ በኋላ ምድር በታላቅ ትኩሳት ይቀልጣል ይላል፡፡ ይህም እሳት ለዘለአለም እንደሚሆን ይነግረናል “ትላቸው ወደማይሞትበት እሳቱም ወደማይጠፋበት” (ማርቆስ 9፡44)፡፡ በዚያ ለዘለአለም ልቅሶና ጥርስ ማፏጨት ይሆናል፡፡ ወደ ኋላ ለሚቀሩት ስቃይና መከራ ይሆንባቸውል፡፡ “የሥቃያቸውም ጢስ ለዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ይወጣል” (ራዕይ 14፡11) ይህ ምን ማለት እንደሆነ ጠባብ አእምሮአችን ሊረደው አይችልም፡፡ የጠፋ፤ የተጣለ! ወደ ፊት የተሸለ ይሆናል የሚል ተስፈ የለም፡፡

ከሁሉ የሚያስከፋው፤ ከትዕቢት እና ከቸልተኝነት፣ ከተድላ ወዳጅነትና ከሀጢአት የተነሳ የዘላለም ህይወት ስጦታን ልናጣው መቻላችን ነው፡፡ ጥፋቱ የራሳችን እንጂ የማንም አይሆንም፡፡ የእግዚአብሔር ፍቅር  ከዘለአለም ሞት እጣ ፈንታ ሊያስመልጠን የደህንነትን መንገድ ስላዘጋጀልን ሁልጊዜ መዳን እንችል እንደነበረ አውቀን በምርጫችን በገሀነም እንሆናለን፡፡

ከ ዮሀንስ 3፡16-17 ስለ እግዚአብሔር ፍቅር የተሻለ ማብራሪያን ሊሰጥ የሚችል የለም፡፡ “በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።ዓለም በልጁ እንዲድን ነው እንጂ፥ በዓለም እንዲፈርድ እግዚአብሔር ወደ ዓለም አልላከውምና”፡፡ ኢየሱስ ሁሉንም ሰው ወደ ህይወት ይጠራል፤ “እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ።  ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ ከእኔም ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤ቀንበሬ ልዝብ ሸክሜም ቀሊል ነውና”፡፡

በብሉይ ኪዳን ዘመን ሁሉ የነበሩ ሰዎች የኮርማ፣ የጠቦት፣ የፍየል እና የእርግብን ደም በማፍሰስ ለሀጢአት ስርየት እንዲሆንላቸው መስዕዋት ያቀርቡ ነበር፡፡ ለሀጢአት ስርይትን ለማግኘት ሞትና የደም መፍሰስ ብቸኛው መንገድ እንደሆነ ተገንዝበው ነበር፡፡ ኢሳያስ 53 ስለ ኢየሱስ “ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም” ብሎ ይነግረናል፡፡ አዎን፤ ካለንበት ከጥፋት መንገድ ለመመለስ ኢየሱስን እንደ አዳኛችን አድርገን መቀበል አለብን፡፡ የእርሱ ደም ለኛ ሀጢአት ስርየት ሆነ፤ የሄደበትን መንገድ መከተል አለብን፡፡ “ኢየሱስም። እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም” (ዮሀንስ 14፡6)፡፡ “ወደ እኔም የሚመጣውን ከቶ ወደ ውጭ አላወጣውም” (ዮሀንስ 6፡37)፡፡ የእግዚአብሔር ቃል ወደ ኢየሱስ ይጠቁመናል፤ የዓለምን ሀጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ ይለዋል፡፡ መጽሀፍ ቅዱስ ኢየሱስ በምድር ላይ እንዴት እንደኖረ፤ ሸክማቸው የከበደባቸውን እንዴት እንዳሳረፈ፣ የታመሙትን እንደፈወሰ እና ለሞቱት ህይወትን እንደ ሰጠ ይነግረናል፡፡ በመጨረሻም በመስቀል ላይ እንደሞተ ሞትን ድል አድርጎ እንደተነሳም ይነግረናል፡፡ እርሲ ፍጹም የደህንነት መንገድ ሆኖልናል፡፡ ታድያ ይህን ታላቅ የደህንነት መንገድ ቸል ብንል ከእግዚአብሔር ቁጣ እንዴት እናመልጣለን?

የክርስቲያን ሀላፊነት

ከጥቂት ጊዜ በኋላ በምድር ላይ ያለን ቆይታ ያበቃል፡፡ ዋናው ጥያቄ፣ ሀላፊነታችንን ተወጥተናል? ለጠፉ ነፍሳት ስለ ክርስቶስ የመመስከር እድሉን አግኝተን ሳናደርገው ስንቀር አጋጣሚው ያልፈናል፡፡ ያቺ ነፍስ ክርስቶስን ሳታውቅ ወደ ዘለአለም ከተሸገረች ግዴታችንን ተወጥተናል ማለት እንችላለን? ለግድ የለሽነታችን ምን ምላሽ እንሰጣለን?

ጌታ በነብዩ ሕዝቅኤል በኩል እንዲህ ይናገራል፤ “እኔ ኃጢአተኛውንበእርግጥ ትሞታለህ ባልሁት ጊዜ፥ አንተም ባታስጠነቅቀው ነፍሱም እንድትድን ከክፉ መንገዱ ይመለስ ዘንድ ለኃጢአተኛው አስጠንቅቀህ ባትነግረው፥ ያ ኃጢአተኛ በኃጢአት ይሞታል፤ ደሙን ግን ከእጅህ እፈልጋለሁ” (ሕዝቅኤል 3፡18)፡፡ በዚህ ምዕራፍ ላይ ያሉትን አራት ተከታታይ ጥቅሶች አንብብ፡፡ እንነዚህ ጥቅሶች ሊያስፈሩንና ያለብንን ትልቅ ሀላፊነት ሊያስገነዝቡን ይገባል፡፡ እኛ ምስክሮቹ ነን፡፡ ለምድራዊ ነገሮች ያለን አመለካከትና ለመንፈሳዊ ነገሮች ያለን ትጋት ሰዎች ስለ ክርስትና በሚኖራቸው አመለካከት ላይ ተጽኖ ያሳድራል፡፡ በመንፈስ ቅዱስ ሀይል ልንሞላ ያስፈልገናል፡፡ ልባችንም በእግዚአብሔር ፍቅር መሞላት አለበት፡፡ እውነተኛ ምስክሮች እንድንሆን ለሚመፉ ነፍሳት ግድ ሊለን ይገባል፡፡ ብዙ ጊዜ ልባችን እንዲነሳሳ ተግተን ከመጸለይ ይልቅ ይህ እስኪሆን ዝም ብለን እንጠብቃለን፡፡ ክርስቲያን ሆይ ዛሬ፤ በፊታችን ላለው ትግል እራሳችንን እንዴት እናበረታታው? ሀላፊነታችንን እንወጣ ይሆን ወይስ የዘላለም ህይወት ስጦታን እናጣዋለን፡፡ ለጌታ ማድረግ ያለብንን አሁን እናድርግ! “ሊመጣ ያለውም ይመጣል አይዘገይምም” (እብራውያን 10፡37)፡፡

ጌታ ሊመጣ ነው፣ ጊዜው መች እንዲሆን ባናውቅም
በእኩለ ሌሊት አሊያም በጠዋት በቀትርም
ምሽትም ላይ ቢሆን፣ ይመጣል ሊወስደን
እንጠብቀው ይሆን፣ ሁሌም ተዘጋጅተን?

ለተጨማሪ መረጃ ያግኙን

በረሪ የውንጌል ጽሑፎችን (ትራክቶችን) ለማዘዝ